(ይድነቃቸው ከበደ)
–
አዋጁ የዴሞክራሲ መብት ሙሉ በሙሉ የሚገድብ ፣እንዲህም አገሪቷ በወታደራዊ ዕዝ እንድትመራ ያደረግ ከመሆኑ ባለፈ አዋጁን ተገን በማድረግ የዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራ መብት እየተጣሰ እንደሆነ በማሳሰብ ፣አዋጁ ሙሉ በሙሉ እንዲነሳ የሰብዓዊ መብት ተቆርቋሪዎች እና የፖለቲካ ፓርቲዎች አመራር እና አባላት ፣ አንዲሁም የተለያዩ ለጋሽ አገራት እየተጠየቁ የገኛሉ ። ይህ በእንዲህ እንዳለ፣ የተወሰኑ ክልከላዎች በዛሬው ዕለት ተነስተዋል ። እነሱም ፦
–
1ኛ.ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ ማንኛውንም ሰው በቁጥጥር ስር ማዋል እና ያለፍርድ ቤት ትዕዛዝ ብርበራ ማድርግ ተሽሯል ።
–
2ኛ.በሬዲዮ፣ ቴሌቪዥን፣ ጽሑፍ፣ ምስል፣ በፎቶ ግራፍ፣ ቴያትር እና በፊልም የሚተላለፉ መልዕክቶችን ለመቆጣጠር እና ለመገደብ የወጣው እገዳም ተሽሯል
–
3ኛ.የተዘረፉ ንብረቶች በመፈተሽ ለባለቤቶቹ እንዲመለሱ ማድረግ እና የመሳሰሉ እርምጃዎችም ተሽሯል፡፡
–
4ኛ.በመሰረተልማት፣ በፋብሪካዎች እና መስል ተቋማት አካባቢ ከምሽቱ 12 ሰዓት እስከ ንጋቱ 12 ሰዓት ከተፈቀደለት ሰራተኛ በስተቀር ማንኛውንም እንዳይንቀሳቀስ የተላለፈው የሰዓት እላፊ ተሽሯል።
–
የፊታችን መጋቢት 28 ቀን 2009 ዓ.ም የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የሚያበቃበት ቀን እንደሆነ ይጠበቃል ። በአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ ምክንያት በተለያየ ፖሊሲ ጣቢያ ከ3 ወር በላይ ታስረው የነበሩ እስረኞች እየተፈቱ ነው። ይሁን እንጂ እስካሁን ጋዜጠኛ ኤሊያስ ገብሩ ፣የቀድሞ አንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ምክትል ኃላፊ የነበረው አቶ ዳንኤል ሺበሺ እና ጦማሪ እዮኤል ፍስሃ ይህ እንዲሁም፣ ሌሎች እስረኞች ይህ መረጃ ይፋ እስከሆነበት ጊዜ ድረስ በአስቸኳይ አዋጁ ምክንያት በእስር ላይ ይገኛሉ። ጋዜጠኛ አናኒያ ሶሪ ከሁለት ቀን በፊት ከእስር ተፈቷል ።
–
በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የተደነገጉ የተወሰኑ ክልከላዎች ተነሱ
Latest from Same Tags
የኢትዮጵያ ህዝብ ቁጥር ከ108 ሚሊዮን በላይ ደረሠ
(ዘ-ሐበሻ) በአለም ባንክና መሠል አለም አቀፍ ተቋማት በዚህ ሳምንት ይፋ የሆነው መረጃ የኢትዮጵያን ህዝብ ብዛት ከ108 ሚሊዮን በላይ አድርሶታል። በዚህ መሠረት ኦክቶበር 22 ቀን
ከመሠረታዊ ዴሞክራሲያዊ የሥርዓት ለውጥ ውጭ ሌላ መውጫ መንገድ የለም!
February 25, 2018 ጠገናው ጎሹ ሰሞኑን በአገራችን የሆነውና እየሆነ ያለው ፖለቲካዊ እውነታ ሩብ ምዕተ ዓመት የዘለቅንበት እጅግ ፈታኝ ( ወፌ ቆመች ሲባል መላልሶ የመውደቅ
ሲግኒቸር ተዘጋ
(ዘ-ሐበሻ) ሲግኒቸር ለብዙ ኢትዮጵያዊያን እንግዳ ነው፡፡ እንኳን ለኢትዮጰያዊያን በሙሉ ለአዲስ አበቤውም ቢሆን ባዕድ ነው፡፡ ኧረ ለአራት ኪሎው መንግስትም ባዳ ነው፡፡ ሲግኒቸር የታደሉ ባለስልጣናትና ልጆቻቸው እንዲሁም
![](https://amharic.thehabesha.com/wp-content/uploads/2013/07/bulcha_demeksa.jpg)
በኦነግ ምክንያት የታሰሩ የኦሮሞ ወጣቶችም ይፈቱ | ቡልቻ ደመቅሳ
ኦነግ “ኦሮሞ ነፃ መውጣት አለበት” ብሎ ከኢትዮጵያ ጦር ጋር ሲታገል፣ የረገፉና የታሰሩ ወጣቶች ቁጥራቸው በትክክል ባይታወቅም እስከ አሁን በእስር ቤት የሚማቅቁ ቁጥራቸው አያሌ ነው፡፡
![](https://amharic.thehabesha.com/wp-content/uploads/2018/01/84403.jpg)
የሻምቡ ጀግና የኦሮሞ ልጆች ፋሽስት ወያኔን በቃሪያ ጥፊ አጩለውታል!
ከአቻምየለህ ታምሩ ወያኔ የኦሮሞና የአማራን ግንኙነት «መርህ አልባው ግንኙነት» በማለት ያወገዘበት የስራ አስፈጻሚ ኮምቴ መግለጫ ቀለም ሳይደርቅ የሻንቡ ልጆች «አንድ ነን! መቼም አንለያይም! «የኦሮሞ