(ዘ-ሐበሻ) ሲግኒቸር ለብዙ ኢትዮጵያዊያን እንግዳ ነው፡፡ እንኳን ለኢትዮጰያዊያን በሙሉ ለአዲስ አበቤውም ቢሆን ባዕድ ነው፡፡ ኧረ ለአራት ኪሎው መንግስትም ባዳ ነው፡፡ ሲግኒቸር የታደሉ ባለስልጣናትና ልጆቻቸው እንዲሁም አንዳንድ የቅርብ ሰዎች ሲጠቀሙበት የከረሙት ጉዳይ ነው፡፡ ይህ የሸራተን አዲስ ሆቴል ብቻ ቃል ነው፡፡ ለበርካታ አመታት እነ ተካ አስፋው፤ እነ መስፍን ባሪያው፤ እነ አበበ ባልቻ፤ የበረከት ስምኦን ልጆች፤ እነ አቦይ ስብሀት ወዘተ… ወዘተ በሸራተን አዲስ ሆቴል የፈለጉትን ተዝናንተው በልተውና ጠጥተው ምንም ሳይከፍሉ ይወጡ ነበር፡፡ የሚወጡት ደግሞ የተጠቀሙበትን ፈርመው ነበር፡፡ ይህ ስርአት በሸራተነኛ ሲግኒቸር ይባላል፡፡ የሲግኒቸር ፈቃጅ ሼህ አልአሙዲ ነበሩ፡፡ ወደ 79 ሰዎች የሲግኒቸር ተጠቃሚ እንደነበሩ ምንጮቻችን ገልፀውልናል፡፡ ከያዝነው ሳምንት ማክሰኞ ጀምሮ ግን ሲግኒቸር መዘራቱ ታውቋል፡፡ እንደ ውስጥ አዋቂ ምንጮቻችን አንዳንድ የሲግኒቸር ተጠቃሚዎች ወደሆቴሉ ጎራ ብለው ተጠቅመው ሲግኒቸር የለም ሲባሉ እየተነጫነጩም ቢሆን ከፍለው ሄደዋል፡፡
ሲግኒቸር ተዘጋ
Latest from Same Tags
የኢትዮጵያ ህዝብ ቁጥር ከ108 ሚሊዮን በላይ ደረሠ
(ዘ-ሐበሻ) በአለም ባንክና መሠል አለም አቀፍ ተቋማት በዚህ ሳምንት ይፋ የሆነው መረጃ የኢትዮጵያን ህዝብ ብዛት ከ108 ሚሊዮን በላይ አድርሶታል። በዚህ መሠረት ኦክቶበር 22 ቀን
ከመሠረታዊ ዴሞክራሲያዊ የሥርዓት ለውጥ ውጭ ሌላ መውጫ መንገድ የለም!
February 25, 2018 ጠገናው ጎሹ ሰሞኑን በአገራችን የሆነውና እየሆነ ያለው ፖለቲካዊ እውነታ ሩብ ምዕተ ዓመት የዘለቅንበት እጅግ ፈታኝ ( ወፌ ቆመች ሲባል መላልሶ የመውደቅ
![](https://amharic.thehabesha.com/wp-content/uploads/2013/07/bulcha_demeksa.jpg)
በኦነግ ምክንያት የታሰሩ የኦሮሞ ወጣቶችም ይፈቱ | ቡልቻ ደመቅሳ
ኦነግ “ኦሮሞ ነፃ መውጣት አለበት” ብሎ ከኢትዮጵያ ጦር ጋር ሲታገል፣ የረገፉና የታሰሩ ወጣቶች ቁጥራቸው በትክክል ባይታወቅም እስከ አሁን በእስር ቤት የሚማቅቁ ቁጥራቸው አያሌ ነው፡፡
![](https://amharic.thehabesha.com/wp-content/uploads/2018/01/84403.jpg)
የሻምቡ ጀግና የኦሮሞ ልጆች ፋሽስት ወያኔን በቃሪያ ጥፊ አጩለውታል!
ከአቻምየለህ ታምሩ ወያኔ የኦሮሞና የአማራን ግንኙነት «መርህ አልባው ግንኙነት» በማለት ያወገዘበት የስራ አስፈጻሚ ኮምቴ መግለጫ ቀለም ሳይደርቅ የሻንቡ ልጆች «አንድ ነን! መቼም አንለያይም! «የኦሮሞ
በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የተደነገጉ የተወሰኑ ክልከላዎች ተነሱ
(ይድነቃቸው ከበደ) – አዋጁ የዴሞክራሲ መብት ሙሉ በሙሉ የሚገድብ ፣እንዲህም አገሪቷ በወታደራዊ ዕዝ እንድትመራ ያደረግ ከመሆኑ ባለፈ አዋጁን ተገን በማድረግ የዜጎች ሰብዓዊና ዴሞክራ መብት