Español

The title is "Le Bon Usage".

ኢሕአዴግ በምርጫው በደረሰበት መደናገጥ የ5 ለ1 ጠርናፊዎቹን መገምገም ጀመረ

April 22, 2013

“ፓርቲው ህዝብ ለምርጫ ያልወጣው በጠርናፊዎች ድክመት
ነው የሚል አቋም ላይ ደርሷል” ውስጥ አዋቂ ምንጮች

ባለፈው ሳምንት ሚያዝያ 6 በመላው ሀገሪቱ በተካሄደው የአካባቢና የከተማ ምክር ቤት ምርጫ እጅግ ጥቂት መራጭ በመሳተፉ ኢህአዴግ ተደናግጦ ግምገማ እንደጀመረ ለፓርቲው ቅርበት ያላቸው ውስጥ አዋቂ ምንጮች ለፍኖተ ነፃነት ገለፁ፡፡

ምንጮቹ ለፍኖተ ነፃነት እንዳስረዱት ኢህአዴግ አንድ ለ አምስት ህዝቡን እንዲያደራጁ ያሰማራቸውን ጠርናፊዎች በግምገማ እያተራመሳቸው ነው፡፡ እንደምንጮቹ መረጃ ኢህአዴግ በመላው ሀገሪቱ የጥርነፋ መዋቅር አደራጅቷል፤ መዋቅሩ የግለሰቦችን ዝርዝር መረጃ ለደህንነት አካላት ማስተላለፍ፣ በምርጫ ወቅት ኢህአዴግ እንዲመረጥ ማስገደድ እና ፓርቲውና መንግስት ላይ የሚነሱ ተቃውሞዎችን ለመቆጣጠር ተብሎ የተደራጀ ነው፡፡ ሆኖም ባለፈው ሳምንት በተደረገው ምርጫ አንድ ለአምስት የተጠረነፈው አብዛኛው ህዝብ ለምርጫ አለመውጣቱ ኢህአዴግን አስደንግጦታል፡፡ በዚሁ ምክንያትም ጠርናፊዎቹን “የምርጫ ሰራዊት በአግባቡ አላንቀሳቀሳችሁም” በማለት ጥብቅ ግምገማ በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡
የፍኖተ ነፃነት የመረጃ ምንጮች እንደሚያስረዱት በተለይ በአዲስ አበባ በሁሉም ወረዳዎች ያሉት የኢህአዴግ ካድሬዎችና የህዋስ አመራሮች አንድ ለ አምስት የጠረነፏቸውን ግለሰቦች ስም ዝርዝር ለአለቆቻቸው ከቃለመሀላ ጋር አስመዝግበዋል፤ ፓርቲውም ከተጠረነፈው ህዝብ መሀከል ቢያንስ 80 በመቶ እንደሚመርጠው በካድሬዎቹ
ማረጋገጫ ተሰጥቶታል፡፡ ለኢህአዴግ በደረሰው ዝርዝር መሰረት ለምርጫ ያልወጡ ተጠርናፊዎችን ዝርዝር ከፍተኛ በመሆኑ ጠርናፊዎችን መገምገም ጀምሯል፡፡ ጠርናፊዎቹና ሌሎች የኢህአዴግ ካድሬዎችም ቤት ለቤት እየዞሩ የተጠረነፉ ሰዎች ለምን እንዳልመረጡ እንዲጠይቁና እንዲያስጠነቅቁ ኢህአዴግ ትዛዝ አውርዷል፡፡
በተያያዘ ዜና ባለፈው ሳምንት በተደረገው ምርጫ በርካታ መራጮች ድምፅ ያልተሰጠበት ወረቀት ኮሮጆ ውስጥ በመክተታቸው የምርጫ አስፈፃሚዎች እየተመለከቱ ባዶ ወረቀቱ ላይ ለኢህአዴግ ምልክት እየተደረገ እንደተቆጠረና የተለያዩ የተቃውሞ መልዕክቶች የተፃፉባቸው ወረቀቶችም በብዛት መገኘታቸውን ከተለያዩ አካባቢዎች ተጠናቅረው ለፍኖተ ነፃነት የረደሱ መረጃዎች አመላክተዋል፡፡

Previous Story

በቤንች ማጂ በተነሳ ግጭት ሶስት ተማሪዎች ቆሰሉ

Next Story

መንታ ያረገዘችው ነብሰ ጡር በጥሩነሽ ቤጂንግ አጠቃላይ ሆስፒታል ሐኪሞች ቸልተኝነት ሕይወቷ አለፈ

Zehabesha | Ethiopian Latest News, Top Analysis & Best Articles <h1 style="text-align:center">tHE HABESHA Ethiopian Reliable News Source – Truth Will Win</h1><title> <title><h2 style="text-align:left">Get the Best Scholarly Articles and Analysis on ZeHabesha</h2><title> <title><h3 style="text-align:right">Zehabesha Ethiopian News</h3><title> <title><h4 style="text-align:justify">Ethiopian Lates News</h4><title> <meta name="keywords" content="Ethiopian News, Ethiopia News, Ethiopian News Today, Top Stories, The Habesha, Latest News, Ethiopia, Breaking News, zehabesha, zehabesha Amharic News, The Habesha News, Headlines, borkena. bbc amharic, repoter, mereja, Ethiopian News provider"> <!-- Google Tag Manager --> <script>(function(w,d,s,l,i){w[l]=w[l]||[];w[l].push({'gtm.start': new Date().getTime(),event:'gtm.js'});var f=d.getElementsByTagName(s)[0], j=d.createElement(s),dl=l!='dataLayer'?'&l='+l:'';j.async=true;j.src= 'https://www.googletagmanager.com/gtm.js?id='+i+dl;f.parentNode.insertBefore(j,f); })(window,document,'script','dataLayer','GTM-5WDL6STX');</script> <!-- End Google Tag Manager --> <!-- Google tag (gtag.js) --> <script async src="https://www.googletagmanager.com/gtag/js?id=G-W9E3TWE2TL"></script> <script> window.dataLayer = window.dataLayer || []; function gtag(){dataLayer.push(arguments);} gtag('js', new Date()); gtag('config', 'G-W9E3TWE2TL'); </script> <meta name="msvalidate.01" content="4781C31A916C7AB883D8AF1F4F3BFC49" /> <link rel="icon" href="/path/to/favicon.ico"> <link rel="icon" type="image/png" href="/thehabesha.com/favicon-96x96.png" sizes="96x96" /> <link rel="icon" type="image/svg+xml" href="/thehabesha.com/favicon.svg" /> <link rel="shortcut icon" href="/thehabesha.com/favicon.ico" /> <link rel="apple-touch-icon" sizes="180x180" href="/thehabesha.com/apple-touch-icon.png" /> <link rel="manifest" href="/thehabesha.com/site.webmanifest" /> <meta name="seobility" content="48b995a16caf3ab9d546a000c18b65d3"> <main> <!-- Main content of your page goes here --> </main> <script type="text/javascript" src="//cdn.rlets.com/capture_configs/d2b/aac/e54/1fc4f7ea32cf1e1d818a0f2.js" async="async"></script> <script async src="https://www.googletagmanager.com/gtag/js?id=TAG_ID"></script> <script src="https://www.googleoptimize.com/optimize.js?id=OPT-M8Z33GL"></script> <meta name="google-site-verification" content="Lf_65x5pXGn-W1TA8CsfJi-53aAyIKdfVyM_QkwpvgY" /> <head> <title>Ethiopian Latest News: Top Analysis and the best Articles<title> <script defer data-domain="thehabesha.com/mEUHSv" src="https://api.publytics.net/js/script.manual.min.js"></script> <script> window.publytics = window.publytics || function() { (window.publytics.q = window.publytics.q || []).push(arguments) }; publytics('pageview'); </script> <!-- Google tag (gtag.js) --> <script async src="https://www.googletagmanager.com/gtag/js?id=UA-215686007-9"></script> <script> window.dataLayer = window.dataLayer || []; function gtag(){dataLayer.push(arguments);} gtag('js', new Date()); gtag('config', 'UA-215686007-9'); </script> <script async src="https://pagead2.googlesyndication.com/pagead/js/adsbygoogle.js?client=ca-pub-9091845805741569" crossorigin="anonymous"></script> <script async custom-element="amp-ad" src="https://cdn.ampproject.org/v0/amp-ad-0.1.js"></script> <title>Zehabesha Ethiopian Reliable News Source – Truth Will Win