ተወዳጁ አርቲስት ማዲንጎ አፈወርቅ የቀብር ሥነ ስርዓት ነገ መስከረም 19 ቀን 2015 ዓ.ም እንደሚፈጸም የቀብር ሥነ ስርዓቱን ለማስፈፀም የተቋቋመው ኮሚቴ አስታወቀ

September 28, 2022
የቀብር ሥነ ስርአቱ ነገ ከቀኑ 9 ሰዓት ላይ በመንበረ ጸባኦት ቅድስተ ሥላሴ ካቴድራል እንደሚፈፀምም ነው ኮሚቴው የገለጸው፡፡
የቀብር ሥነ ስርዓቱን ለማስፈፀም የተቋቋመው ኮሚቴ በአርቲስቱ መኖሪያ ቤት በሰጠው መግለጫ÷ ነገ በአርቲስቱ መኖሪያ ቤት እንዲሁም በወዳጅነት ፓርክ ከ6 ሰዓት ጀምሮ በመንግሥት ኃላፊዎች፣ በሙያ አጋሮቹ፣ በአድናቂዎቹና ወዳጅ ዘመዶቹ የአስክሬን ስንብት እንደሚካሄድ ገልጿል።
ከቀኑ 10 ሰዓት ጀምሮ በመንበረ ጸባኦት ቅድስተ ሥላሴ ካቴድራል ቤተክርስቲያን ሥርዓተ ቀብሩ እንደሚፈጸምም ተናግሯል።
አርቲስት ማዲንጎ በትላንትናው ዕለት በድንገተኛ ህመም በህክምና ላይ እያለ ሕይወቱ ማለፉ ይታወሳል።
ከአርቲስቱ ህልፈት ጋር ተያይዞ እየወጡ የሚገኙ ሀሰተኛ መረጃዎችን ወደጎን በመተው ለአርቲስቱ ያለንን ክብር እናሳይ ሲልም የቀብር አስፈፃሚ ኮሚቴ መልዕክት አስተላልፏል።
ዘጋቢ፦ ድልነሳ መንግስቴ / አማራ ሚዲያ ኮርፖሬሽን 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

የምንኖረዉ ለዕዉነተኛ ለዉጥ መሆን አለበት

Next Story

የአማራ ዜጎች ከወለጋ የሰው ማረጃ ቄራ በሰላም እንዲወጡ የብልጽግና ፌዴራልና፣ የኦሮሚያና የአማራ ክልላዊ መንግሥቶች ግዴታና ተጠያቂነት አለባቸው

Go toTop