ይህ ሁሉ የፓርላማ ግርግር ፥ አድራሻ ለሌለው የአንድ ደቂቃ ፀሎት ነበርን

July 6, 2022

♦የከተማው ሸኔ አራት ኪሎ ቁጭ ብሎ እያፈነ ይሰውርሃል!!
♦የጫካው ሸኔ እያረደ ይጥልሃል ተናቦ መስራት ይልሃል ይኸው ነው!!


ዶ/ር ቴዎድሮስ ኃ/ማሪያም – የአብን የፅ/ቤት ኃላፊ

የፌዴራል የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ከብዙ እግር ጉተታ በኋላ ዛሬ ሰኔ 29/2014 ዓ.ም በአስቸኳይ ስብሰባ ያሳለፈው ውሳኔ በመላው ዓለም ፊት ሀገራችንን መሳቂያ የሚያደርግ አሳፋሪ ውሳኔ ነው። በተለይም በኦሮሚያ ፣ በቤኒሻንጉልና በሌሎች ክልሎች በግፍ ለሚጨፈጨፈው የአማራ ህዝብ እንደ ታላቅ ታሪካዊ ክህደት የሚቆጠር ነው።

1. “ኢሰብአዊ ድርጊት” ፣ “ኢሰብአዊ ጭፍጨፋ” በማለት በብሔር ማንነት ላይ የተመሠረተ የዘር ፍጅት (genocide) መደረጉን ክዷል ፤
2. ‘ንፁሃን ዜጎች” ፣ “ሲቪል ዜጎች” በሚል ሽፋን የጥቃቱ ቀንደኛ ዒላማ የሆነውን የአማራ ህዝብን ሆን ብሎ ሳይጠቅስ አልፎታል ፤
3. “በተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች” በማለት በተለይ መረን የለቀቀ የዘር ማጥፋት ማዕከል የሆነውን የኦሮሚያንና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልሎችን ሳይጠቅስ ፣ በየክልሉ ጥፋትን በእኩልነት በማከፋፈል አልፏል ፤
4. “ባለፉት 27 ዓመታት የተዘራው የዘር ጥላቻ” የሚለው አሳሳች ሀረግም በአሁኑ ወቅት ከቁጥጥር ውጭ ለሆነው የዘር ማጥፋት ድርጊት ቀንደኛ ተጠያቂ የሆነውን በሥልጣን ላይ ያለውን መንግሥት ነፃ ለማውጣት የታለመ ነው ፤
5. የተፈፀመውን ድርጊት “እጅግ በጣም በመኮነን” ፣ “በጣም በመኮነን” የሚለውም የተለሳለሰ አገላለፅ ሆን ተብሎ ድርጊቱን በጥብቅ ላለማውገዝ የተደረገ ነው ፤
6. ውሳኔው በህግ ተጠያቂ የሚያደርጋቸው “ግለሰቦችን” እንጂ በአሸባሪነት የተፈረጁ የታጠቁ ቡድኖችና የነሱ ሽፋን ሰጭ የሆኑ የፖለቲካና የሚዲያ ድርጅቶችና ተቋማትን አይደለም ፤
7. የሀገሪቱ የመጨረሻ ሥልጣን አካልና አስፈፃሚውን የመቆጣጠር ኃላፊነት ያለበት ፓርላማ የፌዴራሉም ሆነ የክልል መንግሥታት ግዴታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ለመጠየቅ እንኳን አልደፈረም ፤
8. ፓርላማው ጥቃቱን በስሙ ጠርቶ ሳያወግዝ ፣ የብዙ ሺህ አማራዎችን ህይወት እየቀጠፈ ላለው የዘር ማጥፋት ድርጊት ማንንም ተጠያቂ ሳያደርግ ፣ “ዜጎች” እያለ ስምና መልክ ለነፈጋቸው የጥቃቱ ሰለባ ህፃናት ፣ ሴቶችና አቅመ ደካሞች ህይወት የሰንደቅ ዓላማ ዝቅ ማድረግና የብሔራዊ ሀዘን ቀን በመንፈግ ኢሰብአዊ ስብስብ መሆኑን አሳይቷል ፤
9. ይህ በታሪክ እጅግ አሳፋሪ ተደርጎ የሚመዘገብ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የፖለቲካ ተውኔት ፣ ፓርላማው በሀገሪቱ የበላይ ህግ እንደተሰጠው ውክልናውም ሆነ ተጠሪነቱ ለኢትዮጵያ ህዝብ ሳይሆን ለገዥው ፓርቲና መንግሥት መሆኑን በይፋ ይመሰክራል።
ወንድሜ ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ከጀርባህ ለነፃነት ፣ ለፍትህና ለክብር የቆምን ብዙ ሚሊዮን አማሮች አለን ‼️

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

በምሬ ወዳጆ የሚመራው የምስራቅ አማራ ፋኖ መግለጫ አወጣ “ሚሊሻ እንድንሆን እየተጠየቅን ነው”

Next Story

በመንግስት ሚዲያዎች በተላለፈው ፕሮግራም እንደተመለከትሁት የፓርላማ ውይይት ላይ አንስቻቸው የነበሩ 3 የሥነ–ስርዓት አስተያየቶች/ጥያቄዎች ተቆርጠው እንዳይተላለፉ ተደርገዋል

Go toTop