ወለጋው ጥቃት ከመንደር 20 ወደ 21 ተዛምቷል!

July 5, 2022
በቄለም ወለጋ ትናንት ሰኔ 27 ቀን 2014 ዓ.ም. የተፈፀመው ጥቃት አድማሱን በማስፋት፣ ከመንደር 20 ወደ መንደር 21 ተዛምቷል።
ከጭፍጨፋው ተርፈው ወደ ሌላ አካባቢ የሸሹ የአካባቢው ኗሪ እንደገለፁት ሕፃናት፣ ሴቶችና አዛዎንቶችን ጨምሮ ቁጥራቸው በትክክል ያልታወቀ ሰዎች ዛሬም በመንደር 21 ተገድለዋል። ዛሬ ከተጨፈጨፉት መካከል የአርጎባ ማሕበረሰብ ተወላጆችም (በኦነግ/ሸኔ አማራ ነው የሚባሉት) ይገኙበታል።
ኦነግ-ሸኔ ጭፍጨፋውን ከኦሮሞ ልዩ ኃይል ጋር በመናበብ እንደፈፀመውም የአካባቢው ኗሪዎች ተናግረዋል። ታጣቂው ቡድን ወለጋን ከአማራ ብሎም ኦሮሞ ካልሆኑት ሁሉ ለማፅዳት እየሠራ መሆኑንም ከጭፍጨፋው የተረፉ አማሮች ተናግረዋል።
ጨፍጫፊው ኃይል ዘመናዊ የቡድን መሳሪያዎችን ጭምር የታጠቀ እንደሆነም ገልፀዋል።
ዘገባው—-ሰሜን አሜሪካ ባልደራስ
————————————————————————————

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

መንግስት ማንነትን መሰረት አድርገው የሚሰነዘሩ ጥቃቶችን ለማስቆም ተገቢውን እርምጃ በመውሰድ አለበት

Next Story

እያደባ በመስፋፋት ላይ ያለው የዘር ማጥፋት ወንጀል (Creeping Genocide) – በዳዊት ወልደ ጊዮርጊስ

Go toTop