የወለጋው ጭፍጨፋ ከ700 ተሻግሯል

June 22, 2022
በምዕራብ ወለጋ ጊምቢ ዞን ጊምቢ ወረዳ በአማራ ተወላጆች የተፈፀመውን ጭፍጨፋ አስመልክቶ የዞን እና የወረዳው አስተዳዳሪዎች እና አመራሮች “የሟቾቹን አስከሬን ወደ መቃብር ስፍራ አታሰባስቡ ፣ በሞቱበት ስፍራ በጅምላ ይቀበሩ” በሚል ሁሉንም አስከሬን በየቤቱ ጓሮ አፈር እያለበሱ መዋላቸውን ከጭፍጨፋው የተረፉ የቀበሌዋ ነዋሪዎች ለአማራ ድምፅ ተናግረዋል።
የዞኑና የወረዳው አመራሮች ይህንን ትዕዛዝ ያስተላለፉት ጭፍጨፋውን አለም አቀፍ ሚዲያዎች እያራገቡት በመሆኑ የሟቾች ቁጥር በትክክል መታዎቅ የለበትም በሚል መሆኑን ከስፍራው በስልክ ያነጋገርናቸው የሟች ቤተሰቦች ገልፀውልናል።
ዛሬ በቀበሌዋ በሚገኙ ሦስት ጎጦች ውስጥ ከሰባት መቶ በላይ አስከሬን መገኘቱን ነዋሪዎች ተናግረዋል።
ከሟቾቹ ውስጥም የአምስት ቀን ጨቅላ ህፃን ትገኝበታለች ብለዋል ነዋሪዎቹ።
ጎበዜ ሲሳይ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

በአማራ ሕዝብ ላይ እየተፈፀመ ላለው የዘር ማጥፋት ወንጀል (Genocide) መንግስት ሙሉ ኃላፊነቱን ሊወስድ ይገባል!!! (መኢአድ)

Next Story

ቃል በተግባር ይገለጽ – ከተቆርቋሪ ኢትዮጵያውያን

Go toTop