![](http://amharic-zehabesha.com/wp-content/uploads/2022/06/abiy-shirak.jpg)
ብሎ ይጠይቃል፡፡ እርምጃ ለመውሰድ ያመነታ አይመስለኝም፡፡ እርምጃ ለመውሰድ ሞክሯል፡፡ ነገር ግን ፡
1ኛ እርሱ መንግስት ውስጥ ፣ ደህንነት መስሪያ ቤት፣ መከላከያ ውስጥ ፣ እንዲሁም የኦሮሞ ክልል ልዩ ኃይል ውስጥ ኦነጎ አሉበት፡፡ እንቅስቃሴ ለማድረግ ሲወሰን፣ ኦነግ አስቀድሞ መረጃ ይደርሰዋል፡፡ ስለዚህ የአብይ መንግስት ራሱን ኦነግ ስለሆነ፣ ራሱን ማሸነፍ አልቻለም፡፡ ጦርነትን የሚወስደው ደግሞ በዋናናነት ወታደራዊ መረጃ ነው፡፡
2ኛ የወታደራዊ አመራር ብቃት የለውም፡፡ ማውራት እንጂ የጦር ስትራቴጂ አያውቅም፡፡ አንዴ አቁሙ ይላል። አንዲ ቀጥሎ ይላል፡፡ የርሱ የጦር አዝማችነት ታች ያሉ መኮንኖችም ግራ ያጋባበት ሁኔታ ነው ያለው፡፡
3ኛ የፖለቲካ ውሳኔዎቹ ህዝቡን የሚያቅፍ ሳይሆን የሚገፋ፣ አምባገነናዊ በመሆኑ፣ ወጣቶችን ማሰር፣ ማወክ፣ ማሸበር ስለበዛ ነው፡፡ ኦህዴድ ከሕወሃት የባሰ አፋኝ ስለሆነ፣ ኦነግ አራት እጥፍ ጭራቅ ቢሆንም፣ ብዙ ተከታዮችን ለማግኘት ችሏል፡፡ በወለጋ በተለይም በርካታ የወረዳና የዞን አመራሮች ሁለት ኮፍያ ያላቸው ናቸው፡፡ ቀን ቀን የኦህዴድን ኮፍያ ያደርጋሉ፣ ማታ ማታ የኦነኝ ኮፍያ ያደርጋሉ፡፡ አብይ በፖለቲካው ረገድ የሕወሃት ሶስት እጥፍ አፋኝ መሆኑ ቀርቶ ህዝቡን ቢያከብር ኖሮ፣ ኦነግ የትም አትደርስም ነበር፡፡