፡
ሹመቱ የተሰጠው በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ነው፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተጨማሪም፡- አቶ ሄኖስ ወርቁን የነዳጅና ኢነርጂ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፣ አቶ ወንድሙ ሴታ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ፣ አቶ ካሊድ አብዱራሂማን በጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት በሚኒስትር ዴኤታ ማዕረግ የፕሮጀክቶች ክትትል ሃላፊ አድርገው ሾመዋል፡፡
በሌላ በኩል ወ/ሮ መሰረት ዳምጤ የፌዴራል ዋና ኦዲተር መስሪያ ቤት ዋና ኦዲተር እንዲሁም አቶ አበራ ታደሰ ደግሞ ምክትል ዋና ኦዲተር ሆነው በህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት እንዲሾሙ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠይቀዋል፡፡
ንጋቱ ሙሉ/sheger