ብጹእ አቡነ በርናባስ በወያኔ ወራሪ ጦር ታፍነው ተወሰዱ – ጌታቸው ሽፈራው

November 9, 2021
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስትያን የዋግኸምራና የካናዳ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ አቡነ በርናባስ በትግሬ ወራሪ ኃይል ከሰቆጣ ከተማ ታፍነው መወሰዳቸው ምንጮች ገልፀዋል።
አቡነ በርናባስ የትግሬ ወራሪ ኃይል ዋግኸምራን ከወረረ በኋላ ሕዝብን በማስተባበር በትህነግ ዘረፋ ምክንያት ለርሃብ የተዳረጉትን ሲያግዙ መቆየታቸው ታውቋል። የትህነግ ወራሪ ኃይል ሰቆጣ ከተማን ሲዘርፍ ያወገዙት አቡነ በርናባስ ሕዝብ ችግሩን እንዲቋቋም ጥረት ሲያደርጉ መቆየታቸው ከአካባቢው ተፈናቅለው የመጡ ነዋሪዎች ገልፀዋል። የትግሬ ወራሪ ኃይል ዘረፋ የተቃወሙትና ሕዝብን በማስተባበር ችግሮችን ለመቅረፍ ሲሰሩ የቆዩት አቡነ በርናባስ ጥቅምት 26/2014 ዓ/ም በትግሬ ወራሪ ኃይል ታፍነው መወሰዳቸው ታውቋል።
የትግሬ ወራሪ ኃይል የዋግኸምራ ነዋሪዎች ላይ ድብደባ፣ ግድያና እገታ እየፈፀሙ እንደሆነ ተፈናቃዮች ገልፀዋል። ባለሀብቶችን በየቤታቸው እየገቡ በመደብደብ፣ አፍኖ በመውሰድ እንዲሁም በመግደል ሀብትና ንብረታቸውን እንደዘረፉ ምንጮች ገልፀዋል። የትግሬ ወራሪ ኃይል አቡነ በርናባስን አፍኖ ወስዶ ድብደባ ፈፅሞባቸዋል የሚሉ መረጃዎች እንዳሉም ተገልፆአል።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

የድርድሩ ሽር ጉድ ተጨማሪ ጫና ወይስ አዲስ ውደቀት? ሊያደምጡት የሚገባ

Next Story

የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ባካሄደው ስብሰባው ሶስት የውሳኔ ሃሳቦችን መርምሮ አፅድቋል

Go toTop