ወረራው ይቀለበሳል፣ ትህነግ ላንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ – ተነስ ወንድ፣ ሴት፣ ሕፃን፣ ሽማግሌ፣ ወጣት ሳትል ተንቀሳቀስ

November 3, 2021
ትህነግ መላውን የትግራይ ሕዝብ እንዴት ከጎኑ ማሰለፍ ቻለ? በብሄርተኝነት አሳምኖ እና አስገድዶ ልትሉ ትችላላችሁ። ግን ከዚህ የበለጠ ጦርነቱን ሕዝባዊ ያረገበት ዋናው መንገድ ሰሜን ዕዝን እንዳጠቃ የሀይል የበላይነት እንዳለው እና የኢትዮጵያንም ሆነ የኤርትራን ጦር ባጭር ቀናት እንደሚያንበረክክ ገምቶ ነበር። ይህ አልሳካ ሲል እና የአፀፋ ምቱ ጠንክሮበት ለመሸሽ ሲገደድ ወያኔ በቀጥታ
  •  ማንኛውንም የመንግስት እና የግል ተቋም እያወደመ ነው የሸሸው
  • መንገዶችን፣ ትምህርት ቤቶችን፣ ኮሌጆችን፣ የጤና ተቋማትን፣ ዩኒቨርሲቲዎችን፣ የመብራት መስመሮች፣ የቴሌ ሰርቨሮችን፣ ባንኮችን ከመዝረፍ አልፎ አውድሞ ነው የሸሸው
  • የመከላከያን እና የኤርትራን ጦር ዩኒፎርም ታጣቂዎቹን አልብሶ የትግራይን ሕዝብ መግደል፣ እናቶቹን እና እህቶቹን መድፈር፣ ንብረቶችን መዝረፍ፣ የሕዝቡን ኑሮ በማመሰቃቀል እና ለቸነፈር እንዲጋለጥ በማድረግ ነው። ይህን ሁሉ ክፋት በሕዝቡ ላይ እየፈጸመ መከላከያን እና የኤርትራን ጦር ተጠያቂ ያደርጋል። ይከሳል ይጮሀል።
ይሄን ክፍተት ለመጠቀም ጊዜ ማባከን ያልፈለጉት ቋሚ ጠላቶቻችን እነ ግብፅ ካፍ ካፉ እየተቀበሉ ክሱን ያስተጋቡለት ጀመር። የኢትዮጵያ መንግስት የምዕራባዊያንን ጫና ለመቀነስ፣ የህወሓትን ተፈጥሮአዊ ባህሪ ለማሳየት ጭምር ( የኔ ግምት ነው) ጦሩን ከትግራይ አውጥቶ የተናጠል የቶግስ አቁም አውጆ ትግራይን ለቆ ወጣ። ትህነግም ሸሽቶ ከተቀረቀረበት ዋሻ በመውጣት ከሕዝቡ ጋር ተፋጠጠ። እንደመንግስትም እንደ መሪም መቀጠል የሚችልበት አቋም ላይ ያልሆነው ጁንታ በሕዝቡ ደካማ ጎን ገባ።
ተነስ ወንድ፣ ሴት፣ ሕፃን፣ ሽማግሌ፣ ወጣት ሳትል ተንቀሳቀስ አለው። ባንክ የለ፣ ኔቶርክ የለ፣ ንግድ የለ፣ ትምርት የለ፣ ደሞዝ የለ፣ አበል የለ? መጀመሪያኑ ይህ እንዲሆን አመቻችቷል። ተነስ ይሄን ያረገህን ውረር፣ ዝረፍ፣ ብሎ ለተወራሪው ስም ሰቶ አሰለፈው። በሕዝብ ማዕበል ወረራ ጀመረ፣ አሁንም ቀጥሎበታል። አላማው አራት ኪሎ በመመለስ ሙሉ በሙሉ የሀገሪቱን የመንግስት ስልጣን መቆጣጠር ነው። ይህ ካልተሳካ ሀገሪቱን ማፍረስ ነው። ያሰለፈው ሀይል ከመውረር እና መዝረፍ፣ ባሻገር የጥላቻ ዘረኝነት ካልሆነ የሚያራምደው ርዕዮትም፣ አላማም የለውም። ከተበተነ ተበተነ ነው። ከተመታ ተመታ ነው። ስለዚህ ይህ ሀይል ወደ ማሰቢያው እንዳይመለስ በጥላቻ ፕሮፓጋንዳ ልቦናውን አውሮ እንደከብት ይነዳዋል።
በህዝብ ማዕበል ተወሮ የሚዘረፈው፣ የሚገደለው የሚፈናቀለው፣ ባልበደለው? በማያውቀው የበቀል ማወራረጃ የሆነው ሕዝብ፣ እራስን የመከላከል ተፈጥሮአዊ መብቱን መጠቀም ሲጀምር ውጤቱ ትህነግ ቀምሮ ከሄደበት በተቃራኒው ይሆናል። ወረራውም ለጊዜው ጉዳትን ያስከትላል እንጂ ባጭር ጊዜ ይቀለበሳል። የጠላትህን የጭካኔ ጥግ ካየህ አንተም የግድ ላለመጥፋት ጭካኔን ከሱ ትማራለህ። አንተን ለማጥፋት በሚመዘው ሰይፍ ትሰይፈዋለህ፣ ላለመሞት መግደል ትጀምራለህ። እንተን በመውረር ሊያጠፋህ የወረረህ ጠላት፣ እሱን እንዴት ማጥፋት እንደምትችል ጭካኔውን ያስተምርሀል። እየሆነ ያለውም ይሄው ነው።
ወረራው ይቀለበሳል፣ ትህነግ ላንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ከምድረ ገፅ የሚያጠፋውን ጭካኔ አስተምሮናል። በሄደበት መንገድ ተጉዞ ትህነግን ማጥፋት ዋጋ ቢያስከፍልም አይቀሬ ነው።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

የአገር መከላከያ ሚስጢራት እየባከኑ ነው – ሰርፀ ደስታ

Next Story

የትግራይ ፓርቲዎች ና የጁንታው አመራሮች – ናትናኤል አስመላሽ

Go toTop