በምዕራብ ሸዋ ዞን ኤጀርሳ ለፎ ወረዳ በደረሰ የተሽከርካሪ አደጋ የስምንት ሰዎች ሕይወት አለፈ

September 26, 2021
በምዕራብ ሸዋ ዞን ኤጀርሳ ለፎ ወረዳ በደረሰ የተሽከርካሪ አደጋ የስምንት ሰዎች ሕይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ። የኤጀርሳ ለፎ ወረዳ ትራፊክ ፖሊስ ተቆጣጣሪ ዋና ሳጂን ፍቃዱ ሙሉጌታ ለኢዜአ እንደገለጹት አደጋው የደረሰው ትላንት ማምሻውን በወረዳው ለገ ሁሉቆ በተባለ አካባቢ ነው።

243158949 3034112716831187 8458959500314486825 n

ከአዲስ አበባ ወደ ጊንጪ ሲጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3– 30485 ኦሮ የሆነ የህዝብ ማመላለሻ ሚኒባስ ከአምቦ ወደ አዲስ አበባ ሲጓዝ ከነበረ ኮድ 3 –52989 ኦሮ የህዝብ ማመላለሻ ቅጥቅጥ አይሱዙ ተሽከርካሪ ጋር በመጋጨቱ አደጋው መድረሱን ተናግረዋል።
በአደጋው የሚኒባሱ አሽከርካሪን ጨምሮ ሚኒባሱ ውስጥ የነበሩ የ8 ሰዎች ህይወት ወዲያው ማለፉንም ተናግረዋል።
በሚኒባሱ እና በአይሱዙ ተሸከርካሪ ውስጥ የነበሩት ጉዳት የደረሰባቸው ስድስት ሰዎች በጳውሎስ ሆሲፒታል ህክምና እየተደረገላቸው መሆኑንም አስረድተዋል፡፡
በአደጋው ህይወታቸው ያለፉ ሰዎች አስከሬን ለየቤተሰቦቻቸው መሰጠቱን የገለጹት ዋና ሳጂን ፍቃዱ የአደጋው መንስኤ እየተጣራ መሆኑንም አስታውቀዋል።
ኢዜአ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

olafscholz spd annalenabaerbock green arminlaschet cdu
Previous Story

የጀርመን ብሔራዊ ምርጫ ወቅታዊ ሁኔታ እና ትንበያ  –  ዋዜማው

242796110 2097044107113593 9066537167633155136 n
Next Story

“የእነሱ ትልቁ ሀይል ዘር ሲሆን የእኛ ትልቁ ሞተራችን ኢትጵያዊነት ነው..” ሌተናል ጄኔራል አበባው ታደሰ

Go toTop