ኢትዮጵያ ዚምባብዌን ባለቀ ሰአት በተገኘ ፍጹም ቅጣት ምት1 ለ0 አሸነፈች

September 7, 2021

የኢትዮጵያ ብሔራዊ የእግር ኳስ ቡድን ለዓለም ዋንጫ ማጣሪያ ዛሬ ከዚምባብዌ ቡድን ጋር ባሕርዳር ስታዲየም ውስጥ ባደረገው ግጥሚያ 1 ለ0 አሸነፈ። ጨዋታው ያለምንም ግብ ሊጠናቀቅ በተቃረበበት 90ኛ ደቂቃ ላይ የተገኘውን የፍፁም ቅጣት ምት አስቻለው ታመነ በግሩም ኹኔታ ከመረብ አሳርፏል።
በዚህም ኢትዮጵያ ከጋና እኩል 3 ነጥብ እና የግብ ክፍያ በመስተካከል ደቡብ አፍሪቃን ትከተላለች። ጋና በሜዳው ባደረገው ግጥሚያ ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያን 1 ለ0 ያሸነፈ ሲሆን፤ ትናንት በደቡብ አፍሪቃ በተራው 1 ለ0 ተሸንፏል። በመጀመሪያው ጨዋታ ዚምባብዌ ከደቡብ አፍሪቃ ጋር ተጋጥማ ያለምንም ግብ ነበር የተለያየችው። በዚህም ደቡብ አፍሪቃ ምድቡን በ4 ነጥብ እና በ1 የግብ ክፍያ ትመራለች።
ኢትዮጵያና ጋና ይከተላሉ፤ ዚምባብዌ የምድቡ የመጨረሻን ደረጃ ይዛለች። የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በአሰልጣኝ ውበቱ አባተ መመራት ከጀመረ ወዲህ ከጠንካራ የአፍሪቃ ቡድኖች ጋር ተጋጥሞ ውጤት በማስጠበቅ እና በማጥበብ መሻሻል ዐሳይቷል።
(ፎቶ፦ ከማኅደራችን)
DW

Leave a Reply

Your email address will not be published.

241388922 1627821567392831 4726832662839271828 n
Previous Story

“አረመኔውና ጨፍጫፊው ትህነግ በሰሜን ጎንደር ዞን ዳባት ወረዳ ጭና ተክለኃይማኖት ቀበሌ ከ100 በላይ ንፁሃንን ጨፍጭፏል” አቶ ግዛቸው ሙሉነህ

Next Story

ብፁዕ ካርዲናል ብርሃነየሱስ የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳሳት የ2014 ዓ.ም የዘመን መለወጫ በዓልን በማስመልከት ለመላው ምዕምናን ያስተላለፉት መልዕክት

Go toTop