የአማራ ክልል መንግስት ህወሃት ወልዲያ ላይ በተኮሰው ከባድ መሳሪያ በንጹሀን ላይ ጉዳት ማድረሱን ገለጸ

August 9, 2021

231224439 573354777452638 1388178489852320492 n

ህወሃት ኃይሎች በአማራ ክልል ላይ ባደረሱት ጥቃት ታሪካዊቷን ላሊበላ ከተማን ጨምሮ ሌሎች የሰሜን ወሎ ቦታዎችን መያዛቸውን ገልጸዋል

የአማራ ክልል የመንግስት ኮሙኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ዋና ዳይሬክተር ግዛቸው ሙሉነህ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ለአል ዐይን ኒውስ በሰጡት ቃለ ምልልስ የህወሀት ታጣቂዎች በወልድያ ከተማ ነዋሪዎች ላይ ከባድ መሳሪያ መተኮሳቸውን ተናግረዋል፡፡

ዋና ዳይሬክተሩ እንዳሉት በአማራ ክልል የሠሜን ወሎ ዞን አስተዳደር ዋና ከተማ በሆነችው የወልድያ ከተማ ከማታ ጀምሮ እስከ ዛሬ አራት ሰዓት ድረስ ከፍተኛ ውጊያ ሲደረግ እንደነበር ገልጸዋል፡፡

ቡድኑ ከከተማዋ በቅርብ ርቀት ላይ ሆኖ ወደ ወልድያ ከተማ ተኮሷዋል ባሏቸው ከባድ መሳሪዎችም በንጹኃን ላይ ጉዳት መድረሱን አቶ ግዛቸው ገልጸዋል፡፡ ትናንትና ምሽት ላይ ህወሃት የተኮሳቸው ከባድ መሳሪዎች ወልድያ ከተማ በሚገኘው ሼክ ሁሴን መሐመድ አሊ አላሙዲን ስታዲዬም እና በሕዝብ መኖሪያ ቤቶች ላይ ማረፉንም አቶ ግዛቸው ተናግረዋል፡፡

ዛሬም ጭምር ተከፍቶ በነበረው ተኩስ በርካታ ጉዳት መድረሱን ያነሱት ዋና ዳይሬክተሩ አሁን ላይ ግን የተወሰነ የተኩስ ፋታ መኖሩን ለአል ዐይን ኒውስ ተናግረዋል፡፡

ወደ ወልዲያ ከተማ በተተኮሱ ከባድ መሳሪያዎች የደረሰው ዝርዝር ጉዳት እስካሁን ባለው ሁኔታ ባይገለጽም በንጹሃን ላይ ግን ጉዳት መድረሱን አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ተናግረዋል፡፡ ህወሃት አሁን ላይ ይዟቸዋል ከተባሉት የአማራ ክልል አካባቢዎች ማስወጣት እንደ አንድ ተግባር ቢያዝም መንግስት ግን ቡድኑን እስከመጨረሻ ለማጥፋት “ቁርጠኛ” መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡

አሁን ለይ የህወሃት ኃይል በሶስት አቅጣጫ ማለትም በባህር ዳር መውጫ፤ በሀራ እና በመርሳ በኩል ተኩስ ቢከፍትም የመንግስት የጸጥታ ኃይሎች በወሰዱት እርምጃ የቡድኑ ተዋጊዎች መገደላቸውን አቶ ግዛቸው አስታውቀዋል፡፡ አሁንም በተወሰኑ ቦታዎች የቀሩ የህወሃት ታጣቂዎች ላይ እርምጃ የመውሰድ ስራው እንደሚቀጥል ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል፡፡

የወልዲያ ከተማ አስተዳደር የኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት፤ በበኩሉ ነሀሴ ሁለት እና ሶስት ቀን 2013 ዓ.ም ከከተማዋ ቅርብ ርቀት ላይ በተደጋጋሚ ከባድ መሣሪያ መወርወሩን ገልጿል፡፡

የወልድያ ከተማ ነዋሪዎች የፌዴራል መንግስት በህዋሀት ቡድን ላይ ፈጣን እርምጃ መውሰድ ባለመቻሉ ቡድኑ ”ከተማዋን ለማውደም ኃላፊነት በጎደለው መልኩ ከባድ መሣሪያ መወርወር ጀምሯል” ማለታቸውን የከተማዋ የኮሙኒኬሽን ጽ/ቤት በይፋዊ የፌስቡክ ገጹ ላይ ብለዋል።

ህወሃት በአማራ ክልል ላይ ባደደረሰው ጥቃት ታሪካዊቷን ላሊበላ ከተማን ጨምሮ ሌሎች የሰሜን ወሎ ቦታዎችን መያዙ ተዘግቧል፡፡

በኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አሸባሪ ተብሎ የተፈረጀው ህወሃት ቃል አቀባይ ጌታቸው ረዳ፤ ቡድናቸው በአማራ ክልል የተለያዩ ቦታዎችን መቆጣጠራቸውን እና በዚህም እስካሁን በሰላማዊ ሰዎች ላይ ጥቃት አለማድረሳቸውን በትዊተር ገጻቸው አስፍረዋል፡፡

ከወራት በፊትየፌደራል መንግስት፣ ህወሃት ሀገረመንግስቱን አደጋ ላይ በሚጥል ተግባር ላይ ተሳትፏል በሚል በህዝብ ተወካዮች ም/ቤት በአሸባሪነት እንዲፈረጅ አድርጓል፡፡

AL ain news agency

 

Leave a Reply

Your email address will not be published.

230885139 2883197801892147 7180770649284854504 n
Previous Story

ማን ያርዳ የቀረበ ማን ይናገር የነበረ ነውና ወንድማችን አርቲስት ዱባለ መላክ በራያ ግንባር ተገኝቶና ተሳትፎ ያየየውንና እየሆነ ያለውን በአሻራ ሚዲያ ቀርቦ ገልጾታል።

235438460 4181630225217958 6745313618171901318 n
Next Story

በአፋር የጁንታው አንድ ክፍለ ጦር ተደምስሷል!!!!!

Go toTop