የማህበራዊ ገጾች አብዮት – ፈ.ፉ.

January 10, 2021

**************************
ጉድ እኮ ነው ይህ ዘመን ይህ ወቅት፣
ወሬዎች እንደ ማዕበል የሚናኙበት፣
እንደ ውሃ ሙላት የሚፈሱበት፡፡
ስንዴው ከእንክርዳዱ ተመስቃቅሎ፣
ልብ አማልሎ ስሜት ሰቅሎ፣
የሚነገር የሚተረክ የቀን ውሎ፡፡
ተቆጣጣሪ ተው ባይ የሌለበት፣
የማህበራዊ ገጽ አብዮት፣
ቅጥ የለሽ፣ ልቅ ጽህፈተ-አንደበት፣
ፌዝ ቁም ነገር የተቀላቀለበት፡፡

ዜና «ሰብሮ» አሉባልታ ገንብቶ፤
የራሱን መስኮተ-ዩ ቱብ ከፍቶ፤
ይመግባል ወሬ ፈትፍቶ፡፡

ምስል ፈብርኮ ወይ ለውጦ፣
እንዲስማማ ከሌላ አውድ መርጦ
ይለቃል ውሸትን እውነትን ገልብጦ፡፡
መፈተሽ ነው ተጠንቅቆ በብልሃት፣
እንዳይለወጥ ሚዛናዊ አስተያየት፣
እንዳይዛባ ፍርድና አመለካከት፡፡
——–
ፈ.ፉ. (10 Jan 2021)

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

በጀርመን የገባውን የኮሮና ቫይረስ ወረርሽኝን በተመለከተ ያለው ቴከኒካዊና ተቋማዊ ልምድና አስተያየት – ክፍል 11

ንግድ ባንክ በብሔር ውስጥ ተዘፍቋል | በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፌስቡክ ላይ በመፃፌ እና በብሔሬ ተባረርኩ አቶ ገነቱ
Next Story

ንግድ ባንክ በብሔር ውስጥ ተዘፍቋል | በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፌስቡክ ላይ በመፃፌ እና በብሔሬ ተባረርኩ አቶ ገነቱ

Go toTop