ኦምሃጅር ከተማ ቀን እየወጣላት ነው

November 30, 2018

በደቡባዊ ምእራብ ኤርትራ የምትገኘውና ሱዳንና ኢትዮጵያን የምትዋሰነው ኦምሃጅር ከተማ ቀን እየወጣላት ነው ተባለ፡፡
የኤርትራ መንግስታዊው የዜና አውታር እንደዘገበው ይህች ከተማ ወደ9500 ያህል ነዋሪዎች ያሏት ስትሆን በአሁኑ ወቅት በሰቲት ድልድይ አማካኝነት ኢትዮጵያና ኤርትራን እያገናኘች ነው፡፡

የከተማዋ ነዋሪዎችም በአዲሱ የኢትዮ ኤርትራ ግንኙነት ከማንም በላይ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚ እንደሚሆኑ ተስፋ መሰነቃቸው ተዘግቧል፡፡ ለአካባቢው ነዋሪዎች መስኖ እርሻ እንዲያገለግል ታስቦ ከ8 አመት በፊት ባደሚት የተባለ ግድብ የተሰራላት ኦምጁሃር እስካሁን የኤሌክትሪክ ሀይል ተጠቃሚ ባትሆንም መንግስት አሁን ካላት ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ አንፃር በጣም በቅርቡ መብራት እንደሚያስገባለትም ተነግሯል፡፡
https://www.youtube.com/watch?v=cKOwRaexXZ4&t=4s

Previous Story

በደቡብ ክልል 42 ሚሊዮን 284 ሺ 908 ብር ጎደለ

Next Story

በመቱ ከተማ ሰልፍ ተካሄደ | በቤኒሻንጉል 66 ሰዎች በፌደራል ፖሊስ በቁጥጥር ስር መዋላቸው ተገለጸ

Go toTop