በሸዋሮቢት በንፁሃን ላይ የመንግሥት ታጣቂዎች በከፈቱት ተኩስ የተሰው ሰዎች ቁጥር ከጊዜ ጊዜ እየጨመረ ነው

July 2, 2022
 ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ሰባት ሰዎች መሰዋታቸው ይፋ ሆኗል።
ከጤና ተቋማት እየወጡ ያሉ ምስጢራዊ መረጃዎች እንደሚያሳዩት ደግሞ፣ የሟቾች ቁጥር ወደ 12 ከፍ ሊል ይችላል። ከሃያ በላይ ቁስለኞችም በመታከም ላይ ናቸው።
“የመንግሥት ታጣቂዎች ቁስለኛ ለማሳከም የሄደን ሰው ሁሉ በጥይት ገድለዋል። ባጃጅ ውስጥ ነው የገደሏቸው። ሕዝቡ እያለቀሰ ነው” ብለዋል ያነጋገርናቸው የዓይን ምስክር።
“መንግሥት መምራት አቅቶታል። የሕዝቡን ጥያቄ መመለስ ባይችል እንኳን፣ ማወያያት ሲገባው በንፁሃን ላይ ተኮሰ። የመንግሥት እንቅስቃሴ ከዕለት ወደ ዕለት የሕዝቡን ቁጣ እየጨመረው ነው” በማለትም ያነጋገርናቸው የመረጃ ምንጭ ጨምረዋል።
አገዛዙ በሸዋሮቢት ተኩሶ የገደላቸውን ሰዎች ለመደበቅና ቁጥሩን ለማሳነስ እየሞከረም ይገኛል።
ዘገባው—-ሰሜን አሜሪካ ባልደራስ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

ከትግራይ የመጡ የሽብር ቡድኑ አባላት በቁጥጥር ሥር ዋሉ

Next Story

አዲስ አበባ ያለው የኦነግ ቢሮ በኦነግ ሸኔ ላይ እየተወሰደ ነው ያለው ወታደራዊ እርምጃ እንዲቆም ጠየቀ

Go toTop