በአሜሪካ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ስልጣን አምባሳደር ኢንጂነር ስለሺ በቀለ የሹመት ደብዳቤያቸውን ለአሜሪካው ፕሬዚዳንት ጆ ባይደን አቀረቡ።
አምባሳደሩ በዚህ ወቅት በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ፀሀፊ አምባሳደር ሞሊ ፊ ጋር በሁለትዮሽ ጉዳዮች ላይ ውጤታማ ውይይት ማድረጋቸውን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ ያመላክታል።
![](http://amharic-zehabesha.com/wp-content/uploads/2022/07/289856109_339987638324698_4353024072721203821_n.jpg)
![](http://amharic-zehabesha.com/wp-content/uploads/2022/07/289644367_339987684991360_8355915671307166140_n.jpg)
ከዚህ ባለፈም የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ባዘጋጁት መርሐ ግብር ላይ ታድመዋል።
![](http://amharic-zehabesha.com/wp-content/uploads/2022/07/289494892_339987788324683_936595752936468460_n.jpg)
(ኢ.ፕ.ድ)