እጅግ አሳዛኝ… ሄዋን ወልዴ ትባላለች የተወለደችዉ ጎንደር ከተማ ነዉ።

March 14, 2022
ሄዋን ከ2008 ዓ ም ጀምሮ ከፋኖ አማራ ጋር አባል ሁና የታገለች የተሰጣትን ተልኮ ሁሉ በአግባቡ የፈፀመች ኢትዮጵያዊን በማዳን እንቅስቃሴ ግንባር ቀደም ጀግና እህታችን ነበረች።
ሄዋን ሁሌም ወደ ማታ ብቻዋን ቤተክርስቲያን የመሳለም ልምድ አላት። በትናትናው ዕለትም አዲስ አለም አካባቢ በሚገኘዉ መስቀለ እየሱስ ቤተክርስቲያን ልታሰለም እንደወጣች ማንነታቸው ባልታወቁ ሰወች ተገላ ተገኝታለች።
በጣም ያሳዝናል በጦርነት ሳትሞት መንግስት ባለበት ሀገር ሀገር ሰላም ብላ ቤተክርስቲያን ለመሳለም በሄደችበት በአደባባይ ተገድላለች
በተደጋጋሚ በመላው አማራ ክልል በከፍተኛ ደረጃ ፋኖዎች እየተገደሉ ነው ! እየሞቱ ሀገር ባዳኑ ምላሻቸው ይህ መሆኑ በጣም ያሳዝናል ! አይ ኢትዮጵያ
እህታችን ነብሷን በአፀደ ገነት ያኑርልን

ከ  አፈትላኪ ዜናዎች የተገኘ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

አቶ ወርቁ አይተነው መልዕክት አስተላለፉ

Next Story

ብልጽግና 45 የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ አባላትን በማስመረጥ ጉባኤውን አጠናቀቀ

Go toTop