(ዘ-ሐበሻ) በቅርቡ በሱማሌያና በዳርፉር የሰላም ማስከበር ሥራ ላይ ተሰማርተው የነበሩ 4 የኢትዮጵያ ዓየር ኃይል አብራሪዎች እና የበረራ አስተማሪዎች የግንቦት 7 ንቅናቄን መቀላቀላቸውን ኢሳት በሰበር ዜናው ዘገበ።
የሕወሓት/ኢህ አዴግን አስተዳደር ከድተው ግንቦት 7ትን የተቀላቀሉት እነዚህ የአየር ኃይል ከፍተኛ የጦር መኮንኖች 2ቱ ሻለቃ እንዲሁም ካፒቴኖች እንደሆኑ ስማቸውም እንደሚከተለው ነው…
1፦ ካፒቴን አክሊሉ መዘነ፣
2፦ ካፒቴን ጥላሁን ቱፋ፣
3፦ ካፒቴን ጌቱ ወርቁና
4፦ ካፒቴን ቢንአም ግዛው