በአማራ ክልል የኦሮሚያ ዞን በጎርፍ አደጋ 28 ሰዎች ሞቱ

August 17, 2013

የከሚሴ ከተማ በደህናው ጊዜ። (ፎቶ ከዊከፒዲያ)(ዘ-ሐበሻ) ትናንት ምሽት በኢትዮጵያ ሰዓት አቆጣጠር ከ7 ሰዓት እስከ 9 ሰዓት ካለማቋረጠ በጣለው ከፍተኛ ዝናብ የተነሳ በአማራ ክልል የኦሮሚያ ዞን ከሚሴ ከተማ በደረሰ የጎርፍ አደጋ የ28 ሰዎች ሕይወት ወዲያውኑ ማለፉ ሲዘገብ የሟቾች ቁጥር ሊጨምር እንደሚችል የውስጥ አዋቂዎች ለዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ገልጸዋል።

በከሚሴ ከተማ ልዩ ስሙ ቀኖ በተባለ አካባቢ የደረሰው የጎርፍ አደጋ የከሚሴ ከተማን ጨምሮ በዙሪያዋ ያሉ አካባቢዎችን ማጥለቅለቁን የታወቀ ሲሆን የመንግስት ተወካዮች ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ በ19 ሰዎች ላይ ጉዳት መድረሱን ተናግረዋል። ይህን ተከትሎ ሌሎች ታዛቢዎች የሟቾቹን ቁጥር እና የተጎጂዎቹን ቁጥር ከዚህ በላይ ያደርጉታለ።

በዚህ የጎርፍ አደጋ ወደ 300 የሚጠጉ ቤቶች በአደጋው የተጠቁ ሲሆን ከ30 በላይ ቤቶች ደግሞ ሙሉ በሙሉ መውደማቸው ተገልጿል። በሌላ በኩል በደሴ ከተማም እንዲሁ ሸዋበር በሚባለው አካባቢ በደረሰው ጎርፍ የኤሌክትሪክ መሰሶዎች ላይ ጉዳት ከመድረሱም በላይ 3 መጋዘኖች በውሃ መጥለቅለቃቸውን የመንግስት ተወካዮች ገልጸዋል።

Previous Story

Sport: ኢትዮጵያ ዛሬ በሜዳሊያዎች ተንበሸበሸች

Next Story

“ኢሕአዴግ ፖለቲካውን የሚመራው በዕዝ ነው እንጂ በሃሳብ የበላይነት አይደለም” – አቶ ሃብታሙ አያሌው

Latest from Same Tags

የአብርሃ ደስታ የሰሞኑ ምርጥ ዘገባዎች

የህወሓት የኮብልስቶን ፖለቲካ (መቐለ) ======================== የመቐለ ወጣቶች (የዩኒቨርስቲ ምሩቃን) ተደራጅተው በኮብልስቶን ስራ ለመሳተፍ ቢወስኑም የህወሓት መንግስት ሊያስሰራቸው እንዳልቻለ ገለፁ። ወጣቶቹ በኮብልስቶን ስራ ተሰማርተው ስራ

ሁሉም ይናገር ሁሉም ይደመጥ!!

ከአንተነህ መርዕድ እምሩ በድሮ አጠራሩ ሻንቅላ በአሁኑ የጉሙዝ ብሄረሰብ የተማርሁት ትልቅ ነገር አለ። “በትልቆች ጉዳይ ምን ጥልቅ አደረገህ” እየተባልሁ በሚያሸማቅቅ ባህል አድጌ በጉሙዝ ህብረተሰብ
Go toTop

Don't Miss