ስለሺ ደምሴ እና ፈንድቃ የባህል ቡድን በሚኒሶታ የኢትዮጵያን ሙዚቃና ዳንስ አስተዋወቁ (ሙሉውን ቪድዮ ይዘናል)

July 12, 2013

(ዘ-ሐበሻ) በሚኒያፖሊስ ሚኒሶታ The Cedar Cultural Center’s የ”African Summer series” በሚል የተለያዩ የአፍሪካ ሃገራትን ሙዚቃዎችና ባህል ባሳየበት በዚህ የበጋው ወራት ዝግጅቶች ኢትዮጵያን በመወከል አርቲስት ስለሺ ደምሴ (ጋሽ አበራ ሞላ) እና ፈንድቃ የባህል ቡድን ረቡዕ ጁላይ 10 ቀን 2013 በተዘጋጀው ወርክሾፕ ላይ ዝግጅታቸውን በማቅረብ የሃገራቸውን ሙዚቃ፣ ዳንስ እና ባህል አስተዋውቀዋል።
በዚህ በርከት ያሉ የውጭ ሃገር እና ኢትዮጵያውያን ዜጎች በተገኙበት የሙዚቃ ዝግጅት ላይ ስለሺ ደምሴ (ጋሽ አበራ ሞላ) እና ፈንድቃ የአዝማሪ ባህል ቡድን በሚኒያፖሊስ የኢትዮጵያን ሙዚቃና ባህል በሚገርም መልኩ አቅርበው ከታዳሚው አድናቆትን አግኝተዋል። ጋሽ አበራ ሞላ በክራሩ አስቂኝ ግጥሞችን በመደርደር ህዝቡን ሲያዝናናው ያመሸ ሲሆን ፈንድቃዎች ደግሞ በውዝዋዜ፣ ትግርኛውን፣ አማርኛውን፣ ኦሮሚኛውን፣ ወላይትኛውን፣ ጉራጊኛውን እና ሌሎችንም ሲያስነኩት ነበር። ይህ 1:20 ደቂቃ ቪድዮን ዘ-ሐበሻ ቀርጻዋለች። ቪድዮውን ለእረፍት ቀንዎ ማየት ከፈለጉ ይኸው። ላላዩት ቢያሳዩት፤ በተለይም በውጭ ሃገር የሚያድጉ ህጻናትና ወጣቶች ቢያዩት መልካም ነው እንላለን። ወደ ቪድዮው፦

Previous Story

አሜሪካንን ጠላሁዋት + አሜሪካንን ወደድኩዋት = _

Next Story

የማለዳ ወግ. . .ዜጎች ከስራ አጥነትና ከድህነትን ለማምለጥ ይሰደዳሉ ፣ መብት አስከባሪ አላቸው ለማለት ግን አልደፍርም (አልጀዚራ)

Go toTop