(ዘ-ሐበሻ) ታዋቂው ጋዜጠኛ እስከድር ነጋ ዛሬ ከታሰረ 4 ዓመት ሞላው:: እስክንድር በ2004 ዓ.ም መስከረም 3 የታሰረ ሲሆን 4 ዓመቱን በጥንካሬ ደፍኗል::
ጋዜጠኛ እስከንድር በሕወሓት መንግስት 18 ዓመት ተፈርዶበት ይግኛል:: ኢትዮጵያውያን በየጊዜው የዚህን ታዋቂ ፎቶ በመያዝ እንዲፈታ መንግስትን ቢጠይቁም ጆሮ ዳባ ልበስ ተብለዋል::
የጋዜጠኛ እስከንድር ነጋ ባለቤት እና እስር ቤት የተወለደው ልጁ ናፍቆት በአሜሪካ ቨርጂኒያ ይገኛሉ::
ሰርካለም የ እስክንድርን 4 ዓመት እስር ቤት ቆይታ በማስመልከት በፌስቡክ ገጿ የሚከተለውን ጽፋለች::
“እነሆ ዛሬ ድፍን 4 ዓመት!! ከመስከረም 3/2004 ዓ.ም-መስከረም 3/2008!
ለቆምክለት ዓላማ እስር አይደለም የህይወት ዋጋም ካስከፈለህ ፣የአንተ መስዋዕትነት ለሌሎች ፈውስ ከሆነ፣ መቼም በማይሸረሸር አቋሜ ከጎንህ እቆማለሁ!
ውዴ የብቸኝነት ህይወት እንደእሬት ቢመረኝም፣ አልፎ አልፎ ቢፈታተነኝም፣ ምርጫዬ ለራሴ ማድላት ሳይሆን ምርጫህ መሆኑን ቃል እገባልሃለው!! ድል ለነፃነት ናፋቂዎች!!
አንድ ቀን ልጅህን ወይ ታቅፈዋለህ አልያም….”
እስክንድር ነጋ ን ፍቱት