Breaking News: ቴዲ አፍሮ ታሰሮ በ30ሺ ብር ተፈታ

October 13, 2014

አሁን በደረሰን መረጃ የ30000 ሺ ብር ዋስ ድምፃዊው በማቅረቡ ከእስር ተለቁዋል::

ድምፃዊ ቴዲ አፍሮ በፌደራል ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን በቀረበበት ክስ ምክንያት ዛሬ ታስሮ ፍርድ ቤት ቀረበ፡፡ ድምፃዊው የቀረበበት ክስ ከስምንት ዓመት በፊት ከቀረጥ ነፃ ወደ ሃገር ውስጥ የገባችን ቢኤምደብሊው መኪና ገዝቶ ተገቢውን የቀረጥ ክፍያ ሳያጠናቅቅ ወደ ስሙ አዛውሯል የሚል መሆኑን የኢትዮጲካሊንክ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡
ድምፃዊው በዚሁ ክስ መሰረት ዛሬ ረፋድ በአራዳ ምድብ አንደኛ ወንጀል ችሎት ቀርቦ ክሱ ከታየ በኋላ ቀርቦ የዕለቱ ዳኛ 30 ሺህ ብር በማስያዝ በዋስ እንዲፈታ ትዕዛዝ ሰጥተዋል፡፡

Previous Story

‹‹ቀራንዮ፣ መድኃኔዓለም፣ ካህናቱ› (በዳንሄል ክብረት)

Next Story

ደኢህዴን በአጼ ምኒልክ ላይ የሰራው ዶክመንተሪ ኢህአዴግ ውስጥ ቅራኔ ፈጠረ * • በርካታ የብአዴን ካድሬዎች በሰንደቅ አላማ በዓል አልተገኙም

Go toTop