Español

The title is "Le Bon Usage".

የአንድ ለ አምስት ጠርናፊዎች ጭምር አለመምረጣቸው ኢህአዴግን አስደንግጦታል

April 24, 2013

ፍኖተ ነፃነት 

ኢህአዴግ  የሚያዚያ 13 ቀን 2005ዓ.ም. የተደረገውን የአዲስ አበባና የደቡብ ክልል ወረዳዎች ምክር ቤት ምርጫ 1 ለ 5 ጥርነፋ ኃላፊነት የተሰጣቸው ግለሰቦች ግዴታቸውን አልተወጡም በሚል በግምገማ እያስጨነቃቸው መሆኑ ተሰማ፡፡ ቀደም ሲል ሚያዚያ 6 ቀን የተደረገውን የአዲስ አበባ፣ የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደርና  የአካባቢ ምርጫ ከዚህ በፊት ኢህአዴግ የልማት ሰራዊት ሲል ከህዝብ ግብር በሚገኝ ገንዘብ ደመወዝ እየከፈለ ለኢህአዴግ ፖለቲካ ቅስቀሳ እንደሚሰሩ የተቃዋሚ ፖለቲካ ፓርቲዎች አቤቱታ ቢያቀርቡም የ2005ዓ.ም. ምርጫ ላይ ግን ኢህአዴግ እራሱ ማስተባበል ያልቻለውን የምርጫ ሰራዊት በማለት 1 ለ 5 ጥርነፋ ስራ በይፋ አሰርቷቸዋል፡፡ ሆኖም ኢህአዴግ ከጠርናፊዎቹ የጠበቀውን ውጤት እንዳላገኘ ተጠቁሟል፡፡ በዚህም ምክንያት በተለይ በአዲስ አበባ ሳምንቱን ሙሉ እስከ ሚያዚያ 13 ቀን 2005ዓ.ም. ምርጫው እስኪጠናቀቅ የየወረዳ ኃላፊዎችና የጥርነፋ ኃላፊነት የተሰጣቸው የኢህአዴግ አባላት በየቤቱ እያንኳኩ ቃል የገቡላቸውን “ሄዳችሁ ምረጡ” የሚል ትዕዛዝ እየሰጡ እንደነበር ተጠቁሟል፡፡

ጠርናፊዎቹም “የገባችሁትን ቃል አላከበራችሁም” በሚል በተለይ በአዲስ አበባና ደቡብ ክልል  ለሚያዚያ 13ቱ ምርጫ በየቤቱ እየዞሩ እንዲቀሰቅሱና የያዙትን ካርድ ይዘው ሄደው ድምፅ እንዲሰጡ በተሰጣቸው  ትዕዛዝ  መሰረት አልተገበራችሁም በሚል አሁንም ሄዳችሁ በአግባቡ አልቀሰቀሳችሁም፣ ቀደም ሲል ቃል ያስገባችሁትም ቢሆን የውሸት ነው ስለዚህ ተልኳችሁትን አልፈፀማችሁም ሲል ቁጣውን ያወረደባቸው መሆኑንና ወደፊትም እርምጃ ሊወስድባቸው ማሰቡንም የፍኖተ ነፃነት ምንጮቻችን አስታውቀዋል፡፡ ይህንንም ሁኔታ የፍኖተ ነፃነት ጋዜጣ ዝግጅት ክፍል ባልደረባ በተግባር የተመለከተ ሲሆን በተለይ የየወረዳው ሰራተኞች በየቤቱ እያንኳኩ በማስከፈት ወረቀትና እስክሪብቶ ይዘው የትኛው ምርጫ ጣቢያ ነው ካርድ የወሰዳችሁት? ከቤታችሁ ስንት ሰው ካርድ ወስዷል? ከመካከላችሁ ሄዶ ድምፅ ያልሰጠ አለ እያሉ ይናገሩ እንደነበር ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡

በአዲስ አበባ አንዳንድ ወረዳዎች ጠርናፊዎችም ጭምር ድምፅ ለመስጠት አለመሄዳቸው ይበልጥ እንዳበሳጫቸው ምንጮቻችን አስታውቀዋል፡፡ ከዚህና ከውጤቱ ጋር በተያያዘ ያነጋገርናቸው የብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ምክትል ጸሐፊ አቶ ወንድሙ ጎላ በበኩላቸው ምርጫው በሰላም ከመጠናቀቁ በስተቀር የተለየ ነገር የለም፤ ውጤቱን በሚመለከት ውደ ፊት ተጣርቶ ይፋ ይደረጋል ሲሉ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

Previous Story

“ሕፃን ካቦካው – ልጅ ያቦካው ይሻላል” (ለተክለሚካኤል አበበ አስተያየት የተሰጠ ድጋፍ)

Next Story

በቤንች ማጂ በተነሳ ግጭት ሶስት ተማሪዎች ቆሰሉ

Zehabesha | Ethiopian Latest News, Top Analysis & Best Articles <h1 style="text-align:center">tHE HABESHA Ethiopian Reliable News Source – Truth Will Win</h1><title> <title><h2 style="text-align:left">Get the Best Scholarly Articles and Analysis on ZeHabesha</h2><title> <title><h3 style="text-align:right">Zehabesha Ethiopian News</h3><title> <title><h4 style="text-align:justify">Ethiopian Lates News</h4><title> <meta name="keywords" content="Ethiopian News, Ethiopia News, Ethiopian News Today, Top Stories, The Habesha, Latest News, Ethiopia, Breaking News, zehabesha, zehabesha Amharic News, The Habesha News, Headlines, borkena. bbc amharic, repoter, mereja, Ethiopian News provider"> <!-- Google Tag Manager --> <script>(function(w,d,s,l,i){w[l]=w[l]||[];w[l].push({'gtm.start': new Date().getTime(),event:'gtm.js'});var f=d.getElementsByTagName(s)[0], j=d.createElement(s),dl=l!='dataLayer'?'&l='+l:'';j.async=true;j.src= 'https://www.googletagmanager.com/gtm.js?id='+i+dl;f.parentNode.insertBefore(j,f); })(window,document,'script','dataLayer','GTM-5WDL6STX');</script> <!-- End Google Tag Manager --> <!-- Google tag (gtag.js) --> <script async src="https://www.googletagmanager.com/gtag/js?id=G-W9E3TWE2TL"></script> <script> window.dataLayer = window.dataLayer || []; function gtag(){dataLayer.push(arguments);} gtag('js', new Date()); gtag('config', 'G-W9E3TWE2TL'); </script> <meta name="msvalidate.01" content="4781C31A916C7AB883D8AF1F4F3BFC49" /> <link rel="icon" href="/path/to/favicon.ico"> <link rel="icon" type="image/png" href="/thehabesha.com/favicon-96x96.png" sizes="96x96" /> <link rel="icon" type="image/svg+xml" href="/thehabesha.com/favicon.svg" /> <link rel="shortcut icon" href="/thehabesha.com/favicon.ico" /> <link rel="apple-touch-icon" sizes="180x180" href="/thehabesha.com/apple-touch-icon.png" /> <link rel="manifest" href="/thehabesha.com/site.webmanifest" /> <meta name="seobility" content="48b995a16caf3ab9d546a000c18b65d3"> <main> <!-- Main content of your page goes here --> </main> <script type="text/javascript" src="//cdn.rlets.com/capture_configs/d2b/aac/e54/1fc4f7ea32cf1e1d818a0f2.js" async="async"></script> <script async src="https://www.googletagmanager.com/gtag/js?id=TAG_ID"></script> <script src="https://www.googleoptimize.com/optimize.js?id=OPT-M8Z33GL"></script> <meta name="google-site-verification" content="Lf_65x5pXGn-W1TA8CsfJi-53aAyIKdfVyM_QkwpvgY" /> <head> <title>Ethiopian Latest News: Top Analysis and the best Articles<title> <script defer data-domain="thehabesha.com/mEUHSv" src="https://api.publytics.net/js/script.manual.min.js"></script> <script> window.publytics = window.publytics || function() { (window.publytics.q = window.publytics.q || []).push(arguments) }; publytics('pageview'); </script> <!-- Google tag (gtag.js) --> <script async src="https://www.googletagmanager.com/gtag/js?id=UA-215686007-9"></script> <script> window.dataLayer = window.dataLayer || []; function gtag(){dataLayer.push(arguments);} gtag('js', new Date()); gtag('config', 'UA-215686007-9'); </script> <script async src="https://pagead2.googlesyndication.com/pagead/js/adsbygoogle.js?client=ca-pub-9091845805741569" crossorigin="anonymous"></script> <script async custom-element="amp-ad" src="https://cdn.ampproject.org/v0/amp-ad-0.1.js"></script> <title>Zehabesha Ethiopian Reliable News Source – Truth Will Win