ኢትዮጵያዊው ላሊሳ ዲሳሳ ባሸነፈበት የቦስተን ማራቶን ቦምብ ፈነዳ

April 15, 2013

ኢትዮጵያዊው ላሊሳ ዲሳሳ ባሸነፈበት የቦስተኑ ማራቶን ማጠናቀቂያ ቦታ ላይ በፈንዱ ሁለት ቦምቦች ይህ ዘገባ እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ 3 ሰዎች መሞታቸውንና ከ40 በላይ ሰዎች ጉዳት እንደደረሰባቸው ታወቀ።

በዚህ ውድድር ላይ ለአሸናፊነት ሲፎካከሩ የነበሩት ገብረ እግዚአብሄር ገብረማርያም እና ላሊሳ ዲሳሳን ጨምሮ በኢትዮጵያውያኑ ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለ የደረሰን መረጃ ያመለክታል። ላሊሳ ይህን ውድድር ለማሸነፍ 2:10:22 እንደፈጀበትም ታውቋል። በውድድሩም ስመጥሩው አትሌት ገ/እግዚአብሄር 3ኛ ወጥቷል።

በቦስተኑ ማራቶን ላይ ከ27 ሺህ የማያንሱ ሯጮች ተሳትፈዋል። ለዚህ ፍንዳታ እስካሁን ኃላፊነቱን የወሰደ ወገን ባይኖርም ፖሊስ ጉዳዩን እየተከታለ መሆኑን ከትንሽ ሰአታት በፊት በሰጠው መግለጫ አስታወቋል። ዛሬ ሰኞ ኤፕሪል 15 ቀን 2013 ከቀኑ 2፡45 አካባቢ ነው ሁለቱ ቦምቦች በሰከንዶች ልዩነት ውስጥ የፈነዱት።
ይህን ቪድዮ ይመልከቱ፦

Medical workers aid injured people at the finish line of the 2013 Boston Marathon following an explosion in Boston, Monday, April 15, 2013. (AP Photo/Charles Krupa)

 

View slideshow

Previous Story

Hiber Radio: “ከሁሉ አገር በታች ሕግ የሌለበት በደመ ነፍስ የሚመራ አገር የእኛ አገር ብቻ ነው” – ታማኝ በየነ (ቃለምልልስ)

Next Story

ወደ ቤኒሻንጉል ጉሙዝ የተመለሱት ተፈናቃዮች ባዶ ሜዳ ላይ መጣላቸው ታወቀ

Go toTop