የአማራና ሕወሓት ያደራጀው የቅማንት ግጭት ተባብሶ መቀጠሉ ተሰማ

January 13, 2019

የአማራና ሕወሓት ያደራጀው የቅማንት ግጭት ተባብሶ መቀጠሉ ተሰማ:: ስላሬ ፣መተማ ፣ደንቢያ ፣ ቆራ ኮኪት ጭልጋ ፣አብርሃደጅርሃ ወዘተ ግጭቱ እየተባባሰ እንደሆነ ከቦታው የሚመጡ መረጃዎች ይጠቁማሉ::
https://www.youtube.com/watch?v=bmsf7vBqDX8
የቀድሞው የመኢአድ አመራር ለገሰ ወልደሃና እንደገለጹት “ትላንትና ትክል ድንጋይ የሚኖሩ የቅማንት ኮሚቴ ነን የሚሉ ሰዎች ወጣቶችን በማደራጀት ከጎንደር ወደ ሳንጃ ሁመራ የሚደረግ ጉዞን መንገድ በዘግተው ወጣቶችን አግተው እንደነበረ ከአካባቢው ያገኘሁት መረጃ ገልፆልኛል” ብለዋል::

የትግራይ ክልል መንግስት ከትንኮሳ አልፎ ሙሉ ለሙሉ ወደ ጦርነት እየገባ ነው ሲል መቶ አለቃ ማስረሻ ሰጤ ተናገረ:: “በትናንትናው እለት በጎንደር ሽንፋ ከፋኖዎቻችን ጋር ጦርነት ከቅማንት ኮሚቴ ጋር ተቀላቅሎ የገባው የህወሃት ቡድን ሲመታ የትግራይ ተወላጆች መታወቂያዎች ተገኝተዋል” ያለው መቶ አለቃ ማስረሻ ይህንንም መታወቂያ ለሕዝብ ይፋ በማድረግ በማህበራዊ ገጾች ለቆታል::

“ማታ ላይ በዳዛ ከ 30 በላይ የአማራ ቤተሰቦቻችንን ቤት አቃጥለዋል። ሮቢት ላይም አንድ የሙስሊም ወንድማችንን ገንዘብ ካላመጣህ በሚል በጸረ ሰላሙ ቡድን መገደሉን ሰምተናል።” ብሏል::

Previous Story

አፋር ሰመራ ላይ ከኢትዮ ጁቡቲ የሚወስደው መንገድ ተዘግቶ ዋለ

Next Story

በሐዋሳ ከተማ ከትናንት በስቲያ በከተማዋ በኢትዮጵያ ትቅደም ትምህርት ቤት የተደራጁ ወጣቶች የግቢውን አጥር…

Go toTop