(ዘ-ሐበሻ) በሬጌ የሙዚቃ ስልት አጨዋወቱ በበርካቶች ዘንድ አድናቆትን ያተረፈው ድምጻዊ እዮብ መኮንን ባሳለፍነው ቅዳሜ ለህክምና በሄደበት ኬኒያ ናይሮቢ ውስጥ በሚገኝ አጋ-ካሃን የተሰኘ ሆስፒታል ህይወቱ ማለፉን ዘ-ሐበሻ መዘገቧ ይታወሳል። በዚህም መሠረት ዛሬ ከቀኑ በ9ሰዓት በቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ሥርዓተ ቀብሩ በርከት ያሉ አድናቂዎቹ፣ የሙያ አጋሮቹ እና ቤተሰቦቹ በተገኙበት ተፈጽሟል።
“እንደቃል” በተሰኘው ብቸኛና የመጀመሪያ አልበሙ ከፍተኛ ተወዳጅነትን አትርፎ የነበረው ድምፃዊ እዮብ፤ ባሳለፍነው ሳምንት ማክሰኞ ዕለት የእህቱን ልጅ ትምህርት ቤት አስመዝግቦ ከተመለሰ በኋላ የግቢውን በር በማንኳኳት ላይ ሳለ ራሱን ስቶ መውደቁና በዚህ የተነሳም በተገኘበት ስትሮክ ለሞት እንደበቃ በዘ-ሐበሻ በተደጋጋሚ ከታመመበት ጊዜ ጀምሮ ሲዘገብ ሰንብቷል። የጭንቅላት ውስጥ ደም መፍሰስ (stroke) መሆኑ ታውቋል።
በተወለደ በ38 ዓመቱ እሁድ ነሐሴ 12 ቀን 2005 ዓ.ም ምሽት 3፡45 አካባቢ ከዚህ ዓለም በሞት የተለየው ድምፃዊው ድምጻዊው ባለትዳርና የአንድ ልጅ አባት ነበር። በተጨማሪም በቅርቡ ይወጣል ተብሎ የሚጠበቅ የሙዚቃ ስራውን ከ70 በመቶ በላይ አጠናቆ እንደነበር በተለያዩ ሚድያዎች የተዘገበ ሲሆን ለድምፃዊው መታሰቢያ ይሆን ዘንድ የተጠናቀቁትን ሙዚቃዎች ለማሳተም እቅድ እንዳለም ለዘ-ሐበሻ ከደረሰው መረጃ መረዳት ተችሏል።
http://www.youtube.com/watch?v=-G1IXShtPLM
የኢዮብ መኮንን የቀብር ሥነ-ሥርዓት ተፈጸመ
Latest from Same Tags
የሶዶ ፖሊስ ማየት የተሳናቸው ተማሪዎች ላይ ድብደባ ፈጸመ
የደቡብ ክልል ትምህርት ቢሮ ‹‹ስቴት ፈንድ›› በሚል በየወሩ የሚሰጣቸው 340 ብር አሁን ካለው የኑሮ ሁኔታ አንጻር በቂ ባለመሆኑ እንዲጨመርላቸው ለሶዶ ከተማ አስተዳደር ጥያቄ ያቀረቡ
health: ስለኮሌስትሮል ሊያውቁ የሚገባዎት 6 ነገሮች
6. ኮሌስትሮልን በጥቂቱ ኮሌስትሮል የሁሉም እንስሳት ህዋሳት አካል የሆነ የማይሟሟ ነጭ የቅባት አይነት ሲሆን በበርካታ የሰውነት ተግባራት ውስጥ ቁልፍ ስራዎችን ያከናውናል፡፡ ሆርሞን ዝግጅት ውስጥ
የወያኔ ትግሬዎች በጉንደት፤በጉራዕ፤በዶጋሊ፤….ጦርነቶች የሚዋሹት ውሸት ሲመረመር
ጌታቸው ረዳ (ኢትዮጵያን ሰማይ ድረገጽ አዘጋጅ) መጀመርያ በዚህ የአመቱ ምርጥ ብየ በምጠቅሰው ጥቅስ ልጀምር፦”የመሬት ላራሹ” ጩኸት ውጤቱ “መሬት ለነጋሹ” ሆኗል፤ ለገበሬው የታሰበውን መሬት ወያኔ
የአብርሃ ደስታ የሰሞኑ ምርጥ ዘገባዎች
የህወሓት የኮብልስቶን ፖለቲካ (መቐለ) ======================== የመቐለ ወጣቶች (የዩኒቨርስቲ ምሩቃን) ተደራጅተው በኮብልስቶን ስራ ለመሳተፍ ቢወስኑም የህወሓት መንግስት ሊያስሰራቸው እንዳልቻለ ገለፁ። ወጣቶቹ በኮብልስቶን ስራ ተሰማርተው ስራ
ሁሉም ይናገር ሁሉም ይደመጥ!!
ከአንተነህ መርዕድ እምሩ በድሮ አጠራሩ ሻንቅላ በአሁኑ የጉሙዝ ብሄረሰብ የተማርሁት ትልቅ ነገር አለ። “በትልቆች ጉዳይ ምን ጥልቅ አደረገህ” እየተባልሁ በሚያሸማቅቅ ባህል አድጌ በጉሙዝ ህብረተሰብ