አቶ እውነቱ ብላታ የሥልጣን ዕድገት አገኙ

August 21, 2013

የኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለሥልጣን ዳይሬክተር የነበሩት አቶ እውነቱ ብላታ ደበላ ከያዙት ኃላፊነት ተነስተው ከፍ ወዳለው የመንግስት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት ሚኒስትር ዴኤታ ሆነው መሾማቸውን ሰንደቅ ጋዜጣ ከአዲስ አበባ ዘገበ። እንደጋዜጣው ዘገባ አቶ እውነቱ የተሾሙት ቦታ አቶ በከር ሻሌ በአሁኑ ወቅት የገቢዎችና ጉምሩክ ዋና ዳይሬክተር ሆነው የተሾሙት የያዙት ቦታ ሲሆን አቶ በከር ከዚህ ኃላፊነታቸው ተነስተው የአዳማ ከንቲባ ሆነው ከተሾሙ በኋላም ከዘጠኝ ወራት በላይ ቦታው ክፍት ሆኖ መቆየቱ ታውቋል።
ጋዜጣው ዘገባውን ቀጥሎ አቶ እውነቱ ብላታ ቀደም ሲል በኦሮሚያ ክልል የፍትህና ፀጥታ ቢሮ ኃላፊ ሆነው የሰሩ ሲሆን በኋላም በፌዴራል ጉዳዮች ጽ/ቤት በከፍተኛ የኃላፊነት ደረጃ ሲሰሩ ከቆዩ በኋላ በኢትዮጵያ ዱር እንስሳት ልማትና ጥበቃ ባለስልጣን ተሹመው ለአንድ ዓመት ሲሰሩ ቆይተዋል ብሏል።

Previous Story

የቁጫ ሕዝብ ጥያቄ ሕጋዊ ምላሽ እንዲያገኝ ጥሪ እናቀርባለን!!! አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)

Next Story

የድምፃዊ ኢዮብ መኮንን የቀብር ሥነ-ሥርዓት ዛሬ ይፈፀማል

Go toTop