ዛሬ መስከረም 3/2008 እስከንድር ነጋ ከታሰረ 4 ዓመት ሞላው

September 14, 2015

(ዘ-ሐበሻ) ታዋቂው ጋዜጠኛ እስከድር ነጋ ዛሬ ከታሰረ 4 ዓመት ሞላው:: እስክንድር በ2004 ዓ.ም መስከረም 3 የታሰረ ሲሆን 4 ዓመቱን በጥንካሬ ደፍኗል::

ጋዜጠኛ እስከንድር በሕወሓት መንግስት 18 ዓመት ተፈርዶበት ይግኛል:: ኢትዮጵያውያን በየጊዜው የዚህን ታዋቂ ፎቶ በመያዝ እንዲፈታ መንግስትን ቢጠይቁም ጆሮ ዳባ ልበስ ተብለዋል::

የጋዜጠኛ እስከንድር ነጋ ባለቤት እና እስር ቤት የተወለደው ልጁ ናፍቆት በአሜሪካ ቨርጂኒያ ይገኛሉ::

ሰርካለም የ እስክንድርን 4 ዓመት እስር ቤት ቆይታ በማስመልከት በፌስቡክ ገጿ የሚከተለውን ጽፋለች::

“እነሆ ዛሬ ድፍን 4 ዓመት!! ከመስከረም 3/2004 ዓ.ም-መስከረም 3/2008!
ለቆምክለት ዓላማ እስር አይደለም የህይወት ዋጋም ካስከፈለህ ፣የአንተ መስዋዕትነት ለሌሎች ፈውስ ከሆነ፣ መቼም በማይሸረሸር አቋሜ ከጎንህ እቆማለሁ!
ውዴ የብቸኝነት ህይወት እንደእሬት ቢመረኝም፣ አልፎ አልፎ ቢፈታተነኝም፣ ምርጫዬ ለራሴ ማድላት ሳይሆን ምርጫህ መሆኑን ቃል እገባልሃለው!! ድል ለነፃነት ናፋቂዎች!!
አንድ ቀን ልጅህን ወይ ታቅፈዋለህ አልያም….”

እስክንድር ነጋ ን ፍቱት

Previous Story

ሞላ አስገዶም ከኤርትራ የከዱት ከሰባቱ የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች ብቻቸውን በስምንት ላንድ ክሩዘር ከወታደሮች ጋር መሆኑ ተገለጸ፣ አገዛዙ አስቀድሞ ግንኙነት እንደነበረው መግለጹ ለሞራሉ የፈጠረው መሆኑም ተጠቆመ፣ የህወሓት ባለስልጣናት ሲያደርጉት የቆዩትን የስልጣን ሽኩቻ ተከትሎ በደህነቱ መ/ቤት አንዱ የአንዱን ደጋፊ ወደ ማጥቃት መሸጋገራቸው፣ በአገር ቤት የበዓል ገበያው ማሻቀብና የነገሰው ውጥረት መላ ካልተበጀለት አገሪቱን ወደ አደገኛ ሁኔታ ሊከት ይችላል መባሉ፣ የመንግስታቱ ድርጅት ወደ ኢትዮጵያ ለሚሄዱ የውጭ አገር ሰዎች ያወጣው ማስጠንቀቂያ፣ ቃለ መጠይቅ ከቴዲ አፍሮ የፌስ ቡክ ኮንሰርት አዘጋጆች አንዱ እና ከጋዜጠኛ አናኒያ ሶሪ በአገር ቤት ስላለው ሁኔታ እና ሌሎችም

Next Story

ዜጐችን ከቀያቸው ማፈናቀል የልማታዊነት መገለጫ አይሆንም !!

Go toTop