ቴዲ አፍሮ፣ ጃኪ ጎሲ፣ ሸዋንዳኝ ኃይሉ እና ሚካኤል በላይነህ በኢትዮጵያውያኑ እግር ኳስ ጨዋታ ሳንሆዜ ላይ ሥራዎቻቸውን ያቀርባሉ

May 21, 2014

(ዘ-ሐበሻ) በሳንሆሴና ሳንፍራንሲስኮ ቤይ ኤርያ ለ31ኛ ጊዜ በሚደረገው የኢትዮጵያውያን የስፖርት ፌስቲቫል ላይ የሚገኙ ድምጻውያን ከወዲሁ ታወቁ።

ላለፉት 31 ዓመታት ኢትዮጵያውያንን በሰሜን አሜሪካ ሲያገናኝ የቆየው ይኸው የስፖርት ፌስቲቫል ከጁን 29 እስከ ጁላይ 5 ድረስ የሚቆይ ሲሆን ሆቴሎችም ከወዲሁ እየሞሉ እንደሚገኙ ከስፖርት ፌዴሬሽኑ ድረገጽ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

በዘንድሮው ኳስ ጨዋታ ወቅት የተለያዩ የሙዚቃ ኮንሰርቶች የሚደረጉ ሲሆን ከነዚህም መካከል ቴዲ አፍሮ፣ ጃኪ ጎሲ፣ ሸዋንዳኝ ሃይሉና ሚካኤል በላይነህ የሚያቀርቧቸው ኮንሰርቶች ከወዲሁ የሕዝብን ቀልብ ስበዋል።

ሐሙስ ጁላይ 3 ቀን 2013 ቴዲ አፍሮ፣ አርብ ጁላይ 4 ቀን 2014 ጃኪ ጎሲ፣ ቅዳሜ ጁላይ 5 ሚካኤል በላይነህ እና ሸዋንዳኝ ኃይሉ የሙዚቃ ኮንሰርታቸውን በሳንሆዜ ያቀርባሉ።

Previous Story

ጅብ ቲበላህ… በልተኸው ተቀደስ – ከጸጋዬ ገብረ መድኅን አርአያ (የቀድሞው ጦቢያ መጽሄት አምደኛ)  

Next Story

ዕለቱ በታሪክ ውስጥ፡ ልክ ዛሬ ግንቦት 13 መንግስቱ ኃይለማርያም ሃገር ጥለው ወጡ፤ የሻለቃ ደመቀ ባንጃው ገድል

Go toTop