አማራ ሚዲያ ማዕከል/አሚማ
ጥቅምት 30 ቀን 2015 ዓ.ም
“ጋዜጠኛ ዳዊት ከአሜሪካ ወደ አዲስ አበባ የገባው ከአምስት ቀናት በፊት ባሳለፍነው አርብ ሲሆን፤ ከ3 ቀናት በፊት በማኅበራዊ ሚዲያው አዲስ አበባን እንዴት እንዳገኛት እያጋራን ነበር። ከሦስት ቀናት በኋላ ወደ ማተሚያ ቤት የሚገባውን አዲሱ መጽሐፉን አርትዖት ለማጠናቀቅ ደፋ ቀና በሚልበት ወቅት ነው ድንገተኛ እረፍቱ የተሰማው” ሲል ጋዜጠኛ ይድነቃቸው ከበደ አጋርቷል።
ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ ከሩህ መጽሄት እስከ ሞገድ ጋዜጣ፤ ከለገዳዲ እስከ ትንሳ’ኤና አድማስ ሬድዮ ያገለገለ ፤ በሙያው አንቱታን ያተረፈ፣ ላለፉት 30 አመታት ያለማቋረጥ በፕሬስ ህትመት እና በሬዲዮ ዝግጅት ክፍል ውስጥ ዋና አዘጋጅ ሆኖ አገልግሏል ።
እግዚአብሔር ነፍሱን በአብርሀም በይስሀቅ በያዕቆብ አጠገብ ያኑርልን።
ለጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ ቤተሰቦች፣ወዳጅ እና አድናቂዎች ልባዊ መፅናናትን ፈጣሪ ይስጥልን !!
ምንጭ_ጋዜጠኛ ይድነቃቸው ከበደ