በኦሮሚያ መስተዳድር ቄለም ወለጋ ዞን፤ ሮቢት ገበያ ወረዳ ለምለም ቀበሌ ውስጥ በአማሮች ላይ አዲስ ጅምላ ጭፍጨፋ ተፈፅሟል

July 4, 2022
ወለጋ አሁን አማራውን እየጨፈጨፉ ነው፡፡ ሕጻናትንና ሴቶችን ነው በብዛት የሚገድሉት ሰዎች እንደዚህ እያደረጉ ያሉት የኦህዴድ መንግስት ድጋፍ ስላላቸው መሆኑ መርሳት የለብንም ንጹሃን ዜጎችን ፡፡ እነዚ ያንን በማድረጋችው ትንሽ እንኳን አይጸጽታቸውም፡፡ ጀግንነት የሰሩ ይመስል ነው በአድናቆት የሚያወሩት
የአብይ መንግስት የተፈጸመው ጄኖሳይድ እየሆነ ያንን ለመሸፋፈን፣ የሞቱትን ቁጥር በመቀነስ የነዚህ ሰዎች ወንጀልን ለማሳነስ በመሞከር፣ የችግሩን አስከፊነት ለመደባበስ ነው እየሰራ ያለው፡፡
አራት ኪሎ ቁርጠኛ የሆነ፣ የሕዝብ ስቃይ የሚሰማው መንግስት ቢኖር ኖሮ ፣ ለችግኝ ተከላ ያለውን ቁርጠኝነት አንድ አስረኛ እንኳን፣ “ሰው መሞት የለበትም” የሚል ቁርጠኝነት ቢኖረው ይሄ ሁሉ ጄኖሳይድ አይኖርም ነበር፡፡
ጭፍጨፋው ነገም፣ ከሳምንት በኋላም ይቀጥላል፡፡ እነ አብይና ኦህዴዶች የፌዴራል መንግስቱን እስከተቆጣጠሩ ድረስ ፣ በሩዋንዳስ ቱትሲዎች ካክሮች(ትንኝ) ተብለው ይጨፈጨፉ እንደነበረው፣ አማራው በኦሮሞ ክል መጤ፣ ሰፋሪ፣ ነፍጠኛ ተብሎ መጨፍጨፉ ይቀጥላል፡፡
አብይ አህመድ የኦሮሞ ጽንፈኛ ታጣቂዎችን አደብ ከማስገዛት፣ ሰራዊቱን አማራ ክልል ልኮ ሰላማዊ ዜጎች ላይ፣ ፋኖ ላይ ነው ጦርነት የከፈተው፡፡
ወገኖች ከዚህ በኋላ አፈሙዙን ወደ አራት ኪሎ በማድረግ ነው በኦሮሞ ክልል ያለውን አማራውንም ሆነ ሌላውን ማህበረሰብ ማዳን የሚቻለው፡፡

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

ለፖለቲካ ትርፍ መሣሪያ አትሁን – ከገብረ አማኑኤል፤

Next Story

የባልደራስ መግለጫ~~በወለጋ በአማሮች ላይ የተፈፀመውን ጭፍጨፋ በጥብቅ እናወግዛለን

Go toTop