ከባድ ውሳኔ ነው። በህይወት ዘመኔ እንዲህ ዓይነት የነፍስ ትንቅንቅ የሚጠይቅ ውሳኔ ላይ የደረስኩበት አጋጣሚ የለም። ወደፊትም ይኖራል የሚል እምነት የለኝም። አሁን ግን ከባዱን ውሳኔ ወስኛለሁ። ከዚያ በፊት ከራሴ ጋር ዝግ ስብሰባ በተደጋጋሚ አድርጌአለሁ። ከነፍሴ ጋር ተሟግቼአለሁ። የሚቀርቡኝን ወዳጆች አማክሬአለሁ። በመጨረሻም መሆን ይኖርበታል ያልኩትን አድርጌአለሁ። ምርጫ የለኝም።
![](http://amharic-zehabesha.com/wp-content/uploads/2022/06/289584179_7631000313607884_4387515658350668255_n.jpg)
ባልደረቦቼ በርቱ። በEMS በጋራ የጀመርነውን ራዕይ ከዳር እንደምታደርሱት ቅንጣት ታክል አልጠራጠርም። አብሬአችሁ እስከ ደሴቲቱ ባለመዝለቄ አዝናለሁ። የተጀመረው መንገድ አባጣ ጎርባጣ ቢበዛውም በኢትዮጵያዊ ጽናት እንደምትሻገሩት እተማመንባችኋለሁ። አንድ ቀን ዳግም እቀላቀላችሁ ይሆናል። ለጊዜው እኔ ሩጫዬን አቁሜአለሁ። እናንተ ግን ጠንክሩ። ግፉበት። ኢትዮጵያ ከእናንተ ብዙ ትጠብቃለችና።
ለሁሉም ኢትዮጵያን ፈጣሪ ይጠብቅልን። ከመጣባት ክፉ አደጋ ይታደጋት ዘንድ ጸሎቴን እቀጥላለሁ። በጥሞና ጊዜዬም ስለኢትዮጵያ ማሰቤን አላቋርጥም። ሀገሬ ልቤ ውስጥ ናትና ሁሌም፣ የትም አስባታለሁ። በተረፈ ሁላችሁንም አመሰግናለሁ።
በመጨረሻም ኢትዮጵያ ታሸንፋለች። ቸር ሰንብቱ!