አታካብዱ ! “የዝንጀሮ ኩፍኝ“ እንጂ “የዝንጀሮ  ፈንጣጣ“ አይደለም ፣ አውሮፖን የናጣት ወረርሺኝ::

May 24, 2022

መኮንን ሻውል ወልደጊዮርጊስ ( ኤክሰፐርት ክሊኒካል ነርስ )

Monkeypox is a rare disease that is caused by infection with monkeypox virus. – CDC

የዝንጀሮ  ኩፍኝ በመባል የሚታወቀውን እና በመላ ሰውነት ላይ የተቀቀለ ማሽላ የመሠሉ ሆኖም ከማሽላ ተለቅ የሚሉ እባጮችን የሚፈጥረውን    ቫይረስ  በእንሥሣት ላይ በቸደረገ ምርምር ለሠጀመሪያ ጋዜ የተረጋገጠው በመካከለኛውና በምእራብ አፍሪካ በ1958 ዓ/ም እጎአ ነው ። በሽታው በሰው ላይ ለመጀመሪያ ጊዜ የተከሰተው ግን በቀድሞዋ ዛየር በአሁኖ ዲሞክራቲክ ኮንጎ ፤ በ1970 ዓ/ም እጎአ  መሆኑ በዓለም የበሽታ ድርሳን ውሥጥ ተመዝግቧል ። ያውም በቀይ ቀለም ። …

ይኸው በዓለም የበሽታ ድርሳን ውሥጥ በቀይ ቀለም የተመዘገበው ሰበቡ ቫይረሥ የሆነው ህመም እንሆ ዛሬ ግንቦት 7/2022 ዓ/ም በኢንግላንድ  ተከስቶ መላ አውሮፓን እና አሜሪካን እያሥፈራራ ነው ።

ይህ ኩፍኝ መሠል ሆኖም ከኩፍኝ መጠናቸው የጎላ እብጠቶችን በሰውነት በሙሉ ና በብዛት ደግሞ በፊት ገፅ  ላይ የሚፈጥረው እና በትኩሳት ፣ በማንቀጥቀጥ ፣በራሥ ምታት ፣ በጀርባ ህመም ፣ በጡንቻ ህመም ና በጉሮሮ ህመም ፣ ሥሜት የሚታወቀው ወረርሺኝ ይኼን ያህል አሥጊና ለመቆጣጠርም የሚያዳግት መድሃኒት አልባ አይደለም ። ማንም ሰው እውቀትን በእውነት ሊገነዘብ የገባልና ይኽ በወረርሺኝ መልክ የተከሰተው በሽታ ከፈንጣጣ  ጋርም የማይመሣሠል ነው ። ፈንጣጣ ወይም “ አንትራክስ “ በባክቴሪያ የሚመጣ ገዳይ በሽታ ነው ። ሃያላኑ አገሮች በላብራቶሪ አባዝተው  በባዮሎጂ ጦር መሣሪያነት  አከማችተው እንደያዙትም በውሥጥ አዋቂዎች እና በጠርጣሪዎች ይወራል ። እናም ይኽ ፀሐፊ የዝንጀሮ ፈንጣጣ የሚባለው ጩኸት ይቆም ዘንድ አበክሮ ይጠይቃል ። ጫማና ኩፍያ የሆነ ፈፅሞ ከእውነት የራቀ ትርጉም ነውና ።

ይኽ የዝንጀሮ ኩፍኝ በተጨማሪ ፣ ዛሬ እና አሁን አሜሪካ፣ ሲውዲን እሥፔን ፣ ፖርቹጋል እና ኢጣሊያ መከሰቱ ታውቋል ። በድንገት  የወረርሽኙ ተጠቂዎች በተጠቀሱት አገሮች በመከሰቱ ፣ አገራቱ ህመምተኞቹን በየሆሥፒታሎቻቸው አግለው እያከሟቸው ነው ። በሌሎች  የአውሮፓ አገሮችም ወረርሽኙ እንደገባ ይወራል  ።

የወረርሽኙ ዛሬ በአውሮፖና በአሜሪካ መግባት በእግዳነት የሚታይና የሚያሥደነግጥም አይደለም ። ከላይ እንደገለፅኩት ይኽ የዝንጀሮ ኩፍኝ ( Monkey pox ) በማለት ሥም የተሠጠው ወረርሽኝ በ2003 በአሜሪካ ተከስቶ እንደንደነበር ይታወቃል  ። በወቅቱ ከ70 የማይበልጡ ሰዎችንም ይኽ መንኪ  ፖክስ ይዞ ነበር ።

እናም ፣  ይኽ በቫይረሥ የሚመጣ ኩፍኝ መሠል በሽታ በቀላሉ በፀረ ቫይረሥ መድሃኒቶች መታከም የሚችል መሆኑ ጥንትም ይታወቃል ። ( ጥንቃቄ አድርጉ እንጂ ፈንጣጣ በማለት ሐሠተኛ ትርጉም በመሥጠት አታካብዱ )

በቅጡ ለመገንዘብም የዩቲዩቡን ዜና እና የነቢቢሲን ዘገባ መርምሩ ። ይኽ በቫይረስ የሚመጣ ኩፍኝ መሠል  በሽታ ነው ።በቃ ። በዋነኝነት የሚተላለፈው በአይጥ ፣ በአይጠ መጎጥ ና በፍልፈልና በመሣሠሉት እንጂ  በዝንጀሮ አይደለም ። ዝንጀሮ ዋንኛ አሥተላላፊ አይደለም ። ሆኖም የዝንጀሮ ዘመድ አዝማድ ሁሉ  በበሽታው ይያዛል ። ያኔም እርሱ ነበር በ1958 ዓ/ም ጥናት የተካሄደበት ።

” በተያዘ ሰው ላይ ጥናት አልተካሄደምን ? ” በማለት ጥያቄ መጠየቅ ተገቢ ነው ። እንካችሁ መልሱን ።

በዝንጀሮ ኩፍኝ  የተያዘ ሰው ከ 5 እሥከ 21 ቀናት በበሽታው መያዙ ሊረጋገጥ ይችላል ። ወይም የበሽታዎቹ ሥሜቶች በነዚህ ቀናት ይታዩበታል ። በበሽታው መያዙ ከታወቀ በኋላ ከበሽታው ለመዳን እሥከ አራት ሣምንት ሊፈጅበት ይችላል ።

በዝንጀሮ ኩፍኝ የተያዘ ሰው ይኽንን ቫይረሥ በሚያሥነጥስ እና በሚያሥል ጊዜ ሊያሥተላልፍ ይችላል ። ከህመምተኛው የተቀቀለ ማሽላ  ከመሠሉ ፣ ችምችም ካሉ እባጮቸ ጋር መነካካትም በሽታውን ያሥተላልፋል ።  በግብረ ሥጋ ግንኙነት ጊዜም በሽታው ወደጤነኛ ሰው ይተላለፋል ።

ይኽ እንግሊዝና እሥፔንን ጭምር ያዳረሰው የዝንጀሮ ኩፍኝ ” አይነተኛው ቫይረስ ” ምንጩ ፣ በመካከለኛውና በምዕራብ አፍሪካ ነው ። ቢባልም ፣ በእንግሊዝ በወረርሽኙ ከተያዙት  8 ቱ ወደ ካናዳ እንጂ ወደ አፍሪካ ተጉዘው የማያውቁ መሆናቸው ታውቋል ።

እናም ወደፊት ሣይንቲሥቶቹ ተመራምረው የዚህ ቫይረሥ ምንጭ ፣ የአውሮፖና የአሜሪካ ምሥጢራዊ ላብራቶሪ ነው ። ባይሉንም እኛ ሰው ነን እና መጠርጠራችን አይቀርም ።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

የዝንጀሮ በሽታ ምንድነው? ስለ ምልክቶች፣ ስለ ፈንጣጣ ክትባቱ እና ስለሌሎች ማወቅ ያለብዎት

Next Story

በሱዳን ስደተኛ ካምፕ የትህነግ ወታደራዊ ምልመላ ቀጥሏል! (በጌታቸው ሽፈራው)

Go toTop