ማዕቀቡ በተመረጡ ግለሰቦች ላይ ብቻ ተግባራዊ እንደሚደረግ እና የኢትዮጵያ ህዝብን በማይጎዳ መልኩ .

September 17, 2021

242214216 4852479981445983 4007525565469795182 n

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ከትግራይ ክልል ቀውስ ጋር በተገናኘ ተጨማሪ ማዕቀብ እንዲጣል አዘዙ !
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ከትግራይ ክልል ቀውስ ጋር በተገናኘ ተጠያቂ ባደረጓቸው የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት እና የአማራ ክልል ባለስልጣናት ላይ እንዲሁም በህወሓት እና በኤርትራ መንግስት አመራሮች ላይ ተጨማሪ ማዕቀብ እንዲጣል አዘዙ።
ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን ዛሬ በፈረሙት የስራ አስፈጻሚ አካል ትዕዛዝ (executive order ) የትግራይ ክልል ግጭት እንዲራዘም ፤ ለትግራይ ክልል ሰብዓዊ እርዳታ እንዳይቀርብ ያስተጓጎሉ እና የቶክስ አቁም ስምምነት እንዳይደረስ እንቅፋት ሆነዋል ባሏቸው ላይ ተጨማሪ ማዕቀብ እንዲጣል ወስነዋል።
ማዕቀቡ እንዲጣል ያዘዙትም ከላይ ለተጠቀሱት ጉዳዮች ተጠያቂ ናቸው በተባሉ የኢትዮጵያ ፌዴራል መንግስት እና የአማራ ክልል መስተዳደር ባለስልጣናት ላይ፤ እንዲሁም በህወሓትና በኤርትራ መንግስት አመራሮች ላይ እንደሆነ የአሜሪካ መንግስት ያወጣው መግለጫ ያመለክታል።
ተጠያቂ ናቸው የተባሉት የመንግስት ባለስልጣናት እና የህወሓት አመራሮች ማንነት ግን ይፋ አልተደረገም።
ይሁን እንጂ የአሜሪካ የመንግስት ግምጃቤት ከ አገሪቱ የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት ጋር በመተባበር ተጠያቂ መሆን የሚገባቸውን እየለየ ማዕቀቡን ተግባራዊ የማድረግ ኃላፊነት ተሰጥቶታል።
ማዕቀቡ በተመረጡ ግለሰቦች ላይ ብቻ ተግባራዊ እንደሚደረግ እና የኢትዮጵያ ህዝብን በማይጎዳ መልኩ እንደሚተገበር የአገሪቱ መንግስት ያወጣው መግለጫ ያመለክታል።
ከዚህ ቀደም ተመሳሳይ የጉዞ ማዕቀብ በኢትዮጵያ የፌዴራል መንግስት አመራሮች እና የህወሓት መሪዎች ላይ መጣሉ ይታወቃል።
© ሪፓርተር

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

US Air Force: Why It’s The Best

242201506 3027814300794362 7415102565538590134 n
Next Story

አራት የቤተሰብ አባላቶቼ በአሸባሪው ቡድን በግፍ ተገድለዋል

Go toTop