በአሸባሪው ቁንጮ ፃድቃን ገ/ትንሣይ የሚመራው የጠላት ኃይል መመታቱ ተገለጸ

August 20, 2021

tsadikan

ዓርሚ ሁለት የሚባልና በከሀዲው ሜጀር ጄነራል ዮኋንስ፣ በምክትሉ ከሀዲው ማዕሾ በየነ እና ከሀዲው ከበደ ፍቃዱ እንዲሁም በሜካናይዝድ አዛዡ ከሀዲው ኮሎኔል ገ/ስላሴ የተመራው ከፍተኛ ቁጥር ያለው የጠላት ሀይል ድባቅ መመታቱ ተገልጿል፡፡
በግንባሩ የተሰማሩ ሁለት ክፍለ ጦር አዛዦች እንደተናገሩት፣ መንግስት የተናጠል የተኩሥ አቁም እርምጃውን ካነሳ በኋላ ከበላይ በተሠጣቸው ትዕዛዝ መሠረት ጋሸናን ዋና ማዕከል በማድረግ ከዋድላ እስከ ላሊበላ መስመር ላይ የነበረውን የአሸባሪውን ኃይል መደምሠሳቸውን አረጋግጠዋል፡፡
በአሁኑ ሰዓት ጠላት በጀግኖቹ የሠራዊት አባላት፣ ልዩ ኃይል እንዲሁም የሚሊሻ አባላትና የአካባቢው አርሶ አደር ከበባ ውስጥ ሆኖ ይገኛል ነው የተባለው፡፡
ይህ የተዳከመ የጠላት ኃይል በጋሸና፣ መቄት፣ ሙጃ፣ በንፋሥ መውጫ አካባቢዎች እየተመታና እየተበተነ ይገኛል ብለዋል፡፡
በነዚህ አካባቢዎች በጠላት ላይ በተደረገ ጥቃት 3 ድሽቃ፣ 6 ሺህ የድሽቃ ጥይት፣ 87 የዕጅ ቦምብ፣ 229 ክላሽንኮቭ ነፍስ ወከፍ መሣሪያ፣ 5 ሺህ የክላሽ ጥይት፣ 1 የጦርሜዳ መነፅር ሲማረክ፣ በርካታ ቁጥር ያለው የሰው ኃይል እና ጠላት ይጠቀምባቸው የነበሩ 2 መድፎች እንዲሁም አንድ ዙ 23 መደምሰስ መቻሉን ዋና አዛዦቹ ገልፀዋል ሲል የመከላከያ ሰራዊት ገልጿል፡፡
ምንጭ∶- የኢፌዲሪ መከላከያ ሰራዊት

Leave a Reply

Your email address will not be published.

233282478 4697033493661823 162371376343043705 n
Previous Story

የአገር እንድነት እንዲከበር ሰው አይበደል – ጆቢር ሔይኢ ከሁስተን ቴክሳስ

239521100 10225766952631292 8081386319511483446 n
Next Story

የሰሜኑን አገራችን ሁኔታ – ግርማ ካሳ

Go toTop