የመከላከያ፣ የልዩ ሃይል፣ የሚሊሺያ ትኩረት መበታተን፣ሃይል ተበታትኖ ሲሳሳ፡ ለጥቃት ምቹ ማድረግ 2)የኢትዮጵያን ህዝብ በስነ ልቦና ጦርነት መስለብ፣ ማደናገር፣ ማሸበር፣ ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው ማድረግ ። የወታደራዊ ጠቀሜታ የሌላቸውን ቦታዎች በሰው ማእበል መያዝ ናቸው።
ሰሞኑን የጀ/ል ጻድቃን በአፋር የጂቡቲ አዲስ አበና መስመርን ከቆረጠ በኋላ ወደ አዲስ አበባ በድል አድራጊነት ለመግባት ለቢቢሲ የተናገረው ቅዥት በአፋር ክልል ልዩ ሃይል እንዲሁም በባለከዘራው ኮሎኔል ሻምበል በየነ የሚመራው ስራዊት የወያኔን ስራዊት ዶጋ አመድ አደረገ። ውሃ በላው። በሺዎች የወያኔ ትግሬ ጀሌዎች ሙት ሆኑ ፣ መቶዎች ተማኩ። ባለፉት ቀናት ከወልዲያ ተደጋጋሚ ጥቃት የሰነዘረውና የሰው ማእበል የሚጠቀመው የወያኔ ትግሬዎች ድውያን አመራር በደረሰበት ከባድ ሽንፈትና ክስረት ፣ ለጥይት እራት እንዲሆኑ ያሰለፋቸው ሕጻናት በመቶዎች ሙትና ምርኮ መሆን ምንም ቁብ አልሰጠውም። በደቡብ ጎንደርና በወሎ መካከል ጛሽና በሚባል አካባቢ ሌላ ሰራዊት በመሰማራት ጠንካራ መከላከያ ሰራዊትም ሆነ የተጠናከረ የአማራ ልዩ ሃይልና ሚሊሺያ የማትጠበቀዋን ላሊበላን ይዣለሁ ማለቱ ፣ በዋነኝነት የስነ ልቦና ጦርነት እንጂ ከወታደራዊ ስትራቴጄክ ጥቅም አኳያ ብዙ ርቀት የሚያስኬድ አይደለም።
የወያኔ ትግሬዎች ቅዠት ዳግም በጦርነት አዲስ አበባ እንገባለን የሚል ነው። ጌታቸው ረዳም ሆን ፣ በቇማጦች ቤት አንድ ጣት ብርቅ እንደሚባለው ፣ክወያኔ ደንቆሮ ጀነራልና ኮ/ል ተብየዎች መካከል የወታደራዊ ሳይንስ (የመደበኛም ፣ የሽምቁንም) የተሻለ ያውቃል፣ የተሻለ አቅም አለው የሚባልለት ጀነራል ጽድቃን ግልጽ አድርገዋል። የ27 አመቱን የወየኔ ትግሬዎች የበላይነት እናመጣለን፣ አማራን፣ ኦሮሞን፣ ሱማሌን፣ ደቡቡን ዳግም በበታችነት ረግጠን እንገዛለን። የእኛ ወርቅ የሆነው የትግሬ ዘር በበላይነት ኢትዮጵያ ላይ ነግሶ ካልዘረፈ ኢትዮጵያን እንበታትናለን ነው አላማቸው። ከዚህ ውጭ ሊሆን አይችልም፤ ኢትዮጵያ ህዝብ በአርስ አርስ ጦርነት አንድትናጥ፣ እንድትተራመስ ማድረግ ግባቸው ነው። ይህን ጦርነት በሙሉ አሸናፊነት ለመወጣት በስነልቦና ጦርነት ህዝቡን ለመከፋፈል፤ አንዳይተማመን ያልተቋረጠ ዘመቻ በማድረግ ላይ ይገኛሉ ።
ወገን ኢትዮጵያውያን አሁንም ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው እንዳንሆን። ለዳግም ውርደትና ባርነት፣ ወይንም እንደ ሀገር ፣ ህዝብ ህልውናችውን እንዳናጣ፣ ከፍተኛ ጥንቃቄ እናድርግ ። ትኩረታችን ፣ የህዝብን ትኩረት የሚሰጡ፣ ስነ ልቦና የሚገነቡ ተግባራት ላይ እናተኩር። በሶሻል ሚዲያ አንቂዎችም ሆናችሁ የሚዲያ ስራ የምትሰሩ ከታሪክ ተጠያቂነት አታመልጡም ።