Sport: ኢትዮጵያ ለቻን ዋንጫ አለፈች

July 27, 2013

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ደ ደቡብ አፍሪካ እ.አ.አ በ2014 ዓ.ም ለምታስተናግደው የአፍሪካ ሀገሮች ሻምፒዮና (CHAN) ውድድር ለማለፍ የሩዋንዳ አቻውን ኪጋሊላይ በመለያ ምት 6 ለ 5 በሆነ ውጤት አሸንፏል። በመጀመሪያው ጨዋታ አዲስ አበባ ስታዲየምላይ በአስራት መገርሳ ብቸኛ ጎል የሩዋንዳ አቻውን 1 ለ 0 ያሸነፈው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ዋሊያዎቹ የተሻለ እድል ይዘው ነበር ወደ ኪጋሊ የተጓዙት።

በጨዋታው የመጀመሪያው አጋማሽ የተሻለ የጨዋታ እንቅስቃሴ የነበረው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን የነበረ ቢሆንም ተጨማሪ ጎል ማስቆጠር ሳይችሉ 0 ለ 0 የመጀመሪያ አጋማሽ ተጠናቋል። በሁለተኛ አጋማሽ ተመጣጣኝ የሆነ ፉክክር ያደረጉ ሲሆን በ68ኛው ደቂቃ ዋሊያዎቹን ሩዋንዳዎች ጎል አስቆጥረው ጨዋታው በአጠቃላይ 1 ለ 1 በሆነ ውጤት 90ው ደቂቃ ተጠናቋል። ሁለቱን ሀገሮች ለመለየት በተደረገው የመለያ ምት ዋሊያዎቹ 6ለ5 በሆነ ውጤት የደቡብ አፍሪካ ትኬታቸውን ቆርጠዋል።

በፍጹም ቅጣት ምቱ የግብ ጠባቂው ሲሳይ ባንጫ ድንቅ ብቃት የታየበት ነበር። በጨዋታው ላይ ጉዳት የደረሰበት ጀማል ጣሰውን የተካው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ግብ ጠባቂ ሲሳይ ባንጫ ሁለት መለያ ምቶችን በማክሸፉም ከፍተኛ አድናቆትን እየተቸረው ይገኛል።

ጎሎቹን ለማየት ይኸው – ከኢትዮ ቲዩብ፦

Previous Story

ጆሮ ያለው ይሰማል! አይን ያለው ይመለከታል! ጆሮ ኖሮት የማይሰማ፣ ዓይን ኖሮት የማያደምጥስ? – ከድምፃችን ይሰማ

Next Story

ለጸረ ሙስና እና ቤቲን እንከሳለን በማለት ለዛቱ አቃቢያነ ህጎች የቀረበች ቆንጆ ፈተና => ሰምሃል መለስ ዜናዊ

Go toTop