ጋዜጠኛውን ደብድቧል የተባለው አርቲስት ዳንኤል ተገኝ በዋስ ተፈታ

November 26, 2014

(ሰንደቅ ጋዜጣ) ነሐሴ 20 ቀን 2006 ዓ.ም በቦሌ ክፍለ ከተማ ገልፍ ኢዚዝ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ ላይ የግል ተበዳይ በሆኑት ጋዜጠኛ ግዛቸው እሸቱ ላይ የቀላል የአካል ጉዳት አድርሰዋል ተብለው በወንጀል ተጠርጥረው ቦሌ ምድብ በመጀመሪያ ደረጃ 4 ወንጀል ችሎት ሕዳር 16 ቀን 2007 ዓ.ም ቀርበው ጉዳያቸው ተሰምቷል።

የወንጀል ችሎቱ ግራና ቀኝ አከራክሮና የሶስት ምስክሮችን ቃል ካዳመጠ በኋላ ሕዳር 30 ቀን 2007 ዓ.ም ለብይን ቀጠሮ ሰጥቷል።
ከዚህ በፊትም በካራማራ ፖሊስ ጣቢያ ለምርመራ የተጠራው አርቲስት ዳንኤል ተገኝ በቀረቡ ጊዜም በ3ሺ ብር ዋስትና መለቀቃቸው ይታወሳል።

Previous Story

ስለደፈራ፤ ደፈር ብለን ስናወራ (በእውቀቱ ስዩም)

Next Story

በጋምቤላ ክልል ያለው የኤች አይቪ ስርጭት በሀገር አቀፍ ደረጃ ካለው ስርጭት በላይ መሆኑ ተገለፀ

Go toTop