የጅቡቲ ውጪ ጉዳይ ሚኒስትር ማሕሙድ አሊ ይሱፍ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን ሊቀ መንበር ሆነው ተመረጡ

February 16, 2025
 የ59 ዓመቱ ዲፕሎማት ለሚቀጥሉት አራት ዓመታት ኮሚሽኑን እንዲመሩ የተመረጡት ዛሬ በአዲስ አበባ መካሔድ በጀመረው የአፍሪካ ኅብረት ዓመታዊ የመሪዎች ላይ ነው።
አሊ ሞሐመድ ይሱፍ ላለፉት ሥምንት ዓመታት የኮሚሽኑ ሊቀ መንበር የነበሩት ሙሳ ፋኪ ማኅማትን ይተካሉ። ይሱፍ የተመረጡት የኬንያው ጉምቱ ፖለቲከኛ ራይላ ኦዲንጋ እና የማዳጋስካር የቀድሞ የኤኮኖሚ እና የፋይናንስ ሚኒስትር ሪቻርድ ራንድሪያማንድራቶን አሸንፈው ነው።
የአፍሪካ ኅብረት 38ኛ ዓመታዊ የመሪዎች ጉባኤ በአዲስ አበባ ሲጀመር የአንጎላው ፕሬዝደንት ዮዋዎ ሎሬንሶ የዓመቱን የአፍሪካ ኅብረት ሊቀመንበርነት ከሞሪታኒያው ፕሬዝደንት ሞሐመድ ዑልድ ተረክበዋል።
የዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ ቀውስ እና የሱዳን ጦርነት በጉባኤው ትልቅ ትኩረት ከሚሰጣቸው ርዕሰ ጉዳዮች መካከል እንደሚሆኑ ይጠበቃል። አሜሪካ የምትሰጠው ሰብአዊ ርዳታ መቋረጥም የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች ዓመታዊ ጉባኤን ትኩረት የሚስብ ነው።
DW

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

በሰሜን ጎጃም ጎንጂ ቆለላ ወረዳ 13 መምህራን በታጣቂዎች ታግተው መወሰዳቸውን ቤተሰቦች ተናገሩ

Next Story

የኢትዮጵያ ልሒቃን የፖለቲካ ባህል ከእልቂትና ከውድመት አዙሪት እንዴት እንውጣ ?

Go toTop