Sport: የብሔራዊ ቡድናችን አጥቂ ጌታነህ ከበደ ዛሬ ወደ ደቡብ አፍሪካ ተጓዘ

June 28, 2013

ከጥሩነህ ካሳ (የወርልድ ስፖርት ጋዜጣ አዘጋጅ)

የኢትዮጵያ ፕርሚየር ሊግን በኮከብ ግብ አግቢነት እየመራ የሚገኘው ጌታነህ ከበደን ከደቡብ አፍሪካ ክለቦች የቀረበለትን የዝውውር ጥያቄ ተቀብሎ ዛሬ ወደ ደ.አፍሪካ አቅንቷል፡፡ ጌታነህን ለመውሰድ የደቡብ አፍሪካው ሰልቲክ ክለብ ከፍተኛ ፍላጎት አሳይቷል፡፡ በርካታ ደጋፊዎች ያሉት ሰልቲክ ከሌሎች ክለቦች የተሻለ ክፍያ ማቅረቡም ታውቋል፡፡
ጌታነህም በዛሬው ዕለት የጤና ምርመራ ለማድረግ ወደ ደቡብ አፍሪካ ተጉዟል፡፡ የጤና ምርመራውን ማለፍ ከቻለም አዲሱን የኮንትራት ውል ይፈራረማል፡፡ ጌታነህ ከደደቢት ክለብ ጋር ያለው ኮንትራት ውል የፊታችን ሰኔ 30 የሚጠናቀቅ በመሆኑ ዝውውሩን የተሳካ እንደሚሆንም ይጠበቃል፡፡

Previous Story

ጃዋር መሃመድ እና የአማራ ሊሂቃን – ከያሬድ አይቼህ

Next Story

ከ110 በላይ ኢትዮጵያዊያን ባህር ላይ ቀሩ

Go toTop