“አማራ ማስተዋል ጀምሯል። አማራው በአማራነቱ እንዳይደራጅ የሸፈነውን ኢትዮጵያዊነት ግርዶሽ ቀዳዶታል” – መስከረም አበራ

አማራ ከእንግዲህ እንደ ድሮው እየተወቀሰ የእነሱ የስሌጣን መወጣጫ ሆኖ አንገቱን ደፍቶ መኖር አይፈልግም። ነቅቷል። የአማራ ህዝብ ክብሩንና ጥቅሙን የከለከለበትን የኢትዮጵያዊነት ግርዶሽ አአስወግዷል። ይሄንን ስል ኢትዮጵያዊነትን ጨርሶ ጥሏል እያልኩ አይደለም።
አማራ ኢትዮጵያን መውደዱ፣ እንደ አማራ የመጣበትን ፈተና እንዳያሳየው አድርጎ የከለለውን የኢትዮጵያዊነት ግርዶሽ አስወግዷል ማለቴ ነው። አማራው በአማራነቱ እንዳይደራጅ የሸፈነውን ኢትዮጵያዊነት ግርዶሽ ቀዳዶታል። ማስተዋል ጀምሯል። አማራ በጥንቃቄ የትግል ግልፀኝነት ላይ እየደረሰ ነው።
የአማራ ብሄርተኝነት ማደግ ተገንጣይ ብሄርተኞችን አስደንግጧል። የአማራ ብሄርተኝነት በዚህ ፍጥነት ያድጋል ብለው አላሰቡም ነበር። በዚያ ላይ ከጦርነቱ መሳሪያ አትርፏል ብለው ስላሰቡ፣ ቢጨንቃቸው ኢትዮጵያ ኢትዮጵያ ማለት ጀምረዋል። ይሄን የሚሉትም የአማራ መጠናከር አማራን እየረገሙ ወደ ስልጣን መውጣትን ስለሚያስቀርባቸው ነው።

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

ኦነግ ሸኔ አዲስ ያሰለጠነውን የጦር ሰራዊት ያስመረቀ ሲሆን በኦሮሚያ የሰሜኑ ክልል ድል እየቀናኝ ነው አለ (የመረጃ ቪዲዮ)

addis ababa zehabesha
Next Story

ባልደራስ ለእውነተኛ ዲሞክራሲ ፓርቲ ያወጣው ወቅታዊ መግለጫ እንደሚከተለው ቀርቧል

Go toTop