መልዕክት ለዘሐበሻ ድህረ ገጽ አንባባያን

March 9, 2022

ዘሐበሻ ድህረ ገጽ ሰሞኑን በብልጽግና ፓርቲ አመራሮች መካከል የተነሳውን የውስጥ ቅራኔ አስታኮ የአብይ ቡድን ተላላኪ በመሆን አቶ ገዱ አንዳርጋቸውን ነጥሎ የተከፈተው ሥም ማጥፋት አካል እንደሆነ ተደርጎ በስህተት ሲጠቀስ አይተናል። አቶ ገዱን አስመልክቶ በዌብሳይታችን የተጠቀሰው አይነት ተልዕኮ ያነገበ ሥም ማጥፋት ዘመቻ አካል አይደለንም። አላደረግንም።

በቅንነት የዘሐበሻ ዌብሳይት የከፈተው ዘመቻ መስሏችሁ የወቀሳችሁን አንባቢያን ስለ አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ምንም አይነት የስም ማጥፋት ዘመቻ አካል እንዳልሆንን በዚህ ማስታወሻ እንደምትረዱ ትስፋ እናደርጋለን። ዌብሳይትችን እንደ ሁልጊዜው የተለያዩ ነገሮችን እያስተናገደ ለአገር እና ሕዝብ ጥቅም እንጂ ገዢዎችን ለማስደሰት ወይም ለማስከፋት የቆመ አለመሆኑን ዛሬም ለክቡራን አንባቢያን ያሳውቃል።
አልዩ ተበጀ
የዘሐበሻ ዌብሳይት ማኔጂንግ ዳይሬክተር

https://zehabesha.com/contact/

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

“ጊዜና ትውልድ ገና የሚያከብረው ኢትዮጵያዊ” ገዱ አንዳርጋቸው!!

Next Story

ቁማሯን እንዴት ሊበሏት እንዳሰቡ እንመልከት – አራጋው ሲሳይ

Go toTop