በአማራ ክልል ሰርጎ የገባው የአሸባሪው ህወሀት ሀይል መደምሰሱን በሰሜን ወሎ ግንባር የተሰማራው የሰራዊት ክፍል አስታወቀ

August 20, 2021
236244955 3007732859469173 1442007123964492267 n
236244955 3007732859469173 1442007123964492267 n

ነሀሴ 14 -2013 (ኢዜአ)በአማራ ክልል ሰርጎ የገባው የአሸባሪው ህወሀት ሀይል መደምሰሱን በሰሜን ወሎ ግንባር የተሰማራው የሰራዊት ክፍል አስታውቋል ።

ጀግናው የመከላከያ ሰራዊት ዋድላ ወረዳ ፣ ኮን ከተማ እንዲሁም በጋሸና አካባቢ የሚገኘውን የአሸባሪ የህወሀት ቡድን በመምታት አኩሪ የጀግንነት ተግባር መፈጸሙን አዛዥ አረጋግጠዋል ፡፡
ጀግኖቹ የሰራዊት አባላት በአካባቢው የሚገኝ የጠላት ፣
የሰውና የመሳሪያ ሀይል በየትኛውም አቅጣጫ እንዳይወጣ በማድረግና በመደምሰስ ከዋድላ ወረዳ እስከ ጋሸና ከተማ በመቆጣጠር ታሪካዊ ድል መፈፀማቸውን አመልክተዋል፡፡
ሠራዊቱ ከወልዲያ አምልጦ የመጣውን ጠላት
በመከታተል ፣ በዋድላ ወረዳና አካባቢ የመሸገውን የጠላት ሀይል እና መሳሪያ በመደምሰስ በከፍተኛ ድል ጋሸና ከተማን መቆጣጠሩን ከመከላከያ ሰራዊት ያገኘነው መረጃ ይጠቁማል፡፡
የቪዲዮ መረጃዎቻችንን ለማግኘት የኢዜአ ን የዩቲዩብ ቻናል ሰብስክራይብ ያድርጉ
ኢዜአ

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

በእነ ደብረጽዮን ገብረሚካኤል የክስ መዝገብ ፍርድ ቤት የቀረቡ 21 ተከሳሾች የጠየቁት የዋስትና መብት ውድቅ ተደረገ

Next Story

ፍርድ ቤቱ ፌዴራል ፖሊስ በሽብር ወንጀል የተከሰሱትን እነሌተናል ጀኔራል ፃድቃን ገብረ ትንሳኤን ይዞ እንዲያቀርብ ትእዘዝ ሰጠ

Go toTop