![230885137 1605320519642936 7620135922838000905 n](https://amharic.thehabesha.com/wp-content/uploads/2021/08/230885137_1605320519642936_7620135922838000905_n-960x640.jpg)
በሽኝት መርኃግብሩ ላይ ኮሎኔል አለበል አማረ ባደረጉት ንግግር “አብረን ወደ ፊት እንሄዳለን፤ አብረን የጀግንነት ሥራ እንሠራለን” ሲሉ ለፋኖ ሠራዊት ተናግረዋል፡፡
አማራን በማዳከም ኢትዮጵያን ለማፍረስ የውስጥ እና የውጭ ጠላቶች ግብ አድርገው እየተንቀሳቀሱ ነው ያሉት ኮሎኔሉ ይሄንን በጀግንነት ቀልብሰን የአማራን ታሪክ እናድሳለን፤ የኢትዮጵያን ሉዓላዊት እናስከብራለን ብለዋል፡፡
ፋኖ ቤዛዊት አያሌው በህልውና ዘመቻው ከተቀላቀሉ ወጣቶች መካከል አንዷ ናት፡፡ “ፋኖዎች ትግሉን አስበንበት እና ቆርጠን ወጥተናል፤ ጠላት የገባበት ገብተን እንደመስሰዋለን፡፡ ትግሉ ሴት ወንድ ብሎ አይለይም፤ የሁሉም ጉዳይ ነው” ብላለች፡፡