‹‹መንግሥት ለአገር ሕልውና የተጋደሉና ጀብድ የሠሩ ፋኖዎችን ያደራጃል እንጂ ትጥቅ አያስፈታም›› አቶ ግዛቸው ሙሉነህ

January 16, 2022
የአማራ ክልል መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ

gizachew

መንግሥት ለአገር ሕልውናና ለሕዝብ ነጻነት የተጋደሉና ጀብድ የሠሩ ፋኖዎችን የበለጠ ያደራጃል እንጂ ትጥቅ አያስፈታም ሲሉ የአማራ ክልል መንግሥት ኮሙኒኬሽን ቢሮ ኃላፊ አቶ ግዛቸው ሙሉነህ ተናገሩ፡፡

አቶ ግዛቸው ሙሉነህ በተለይ ለኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት እንደገለጹት፤ በአማራ ሕዝብ ታሪክ ውስጥ የአማራን ሕዝብ ከጠላት የሚከላከል፣ ከውርደት የሚታደጉና በልማትና በፖለቲካው መስክ ተጠቃሚ እንዲሆን ዋጋ የሚከፍሉ ሁሉ ፋኖዎች ናቸው፡፡ በመሆኑም መንግሥት ለአገር ሕልውናና ለሕዝብ ነጻነት የተጋደሉና ጀብድ የሠሩ ፋኖዎችን የበለጠ ያደራጃል እንጂ ትጥቅ አያስፈታም ብለዋል፡፡
የአሸባሪው ሕወሓት ቡድንን ወረራ ለመቀልበስ ፋኖዎች ትልቅ ጀብድ ፈጽመዋል፤ የሕይወት መስዋዕትነትም ከፍለዋል ያሉት ቢሮ ኃላፊው፤ መንግሥት ለእነዚህ ሰዎች እውቅና ሰጥቶ ይሸልማል እንጂ ትጥቅ የሚያስፈታበት ምክንያት እንደሌለው ገልጸዋል፡፡
የመንግሥት ሃሳብ ለአገሩ ሲዋደቅ ጉዳት የደረሰበትን ፋኖ ለሌሎች ኃይሎች በሚደረገው አግባብ እንዲታገዝ ፣ ለአገር ክብር ለተሰዋውም ለሌላው እንደተደረገው ማድረግ እንጂ..

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

እኔም ስሰማ በጣም ደንግጫላሁ

Next Story

እንደ ኢትዮጵያዊ ካለፈው ምን ተማርን? ለመጭው ትግልስ የምን ያህል  እየተዘጋጀን ነው? —ፊልጶስ

Go toTop