የአማራ ክልል ወጣቶች የአካባቢያቸውን ሰላምና ደህንነት ነቅተው እንዲጠብቁ ጀነራል አሳምነው ጽጌ አሳሰቡ

January 5, 2019

የአማራ ክልል ወጣቶች የአካባቢያቸውን ሰላምና ደህንነት ነቅተው በመጠበቅ በሃገሪቱ ለተጀመረው የለውጥ እንቅስቃሴ ስኬታማነት ሊሰሩ እንደሚገባ የክልሉ የሰላምና ደህንነት ቢሮ ኃላፊ ብርጋዴል ጀነራል አሳምነው ጽጌ ትናንት ከወልድያ ከተማ ነዋሪዎች ጋር ባደረጉት ውይይት ገለጹ::

https://youtu.be/J8BZqY2t65c

ባለፉት ዓመታት አማራው በክልሉ ውስጥም ሆነ በሌሎች ክልሎች ማንነቱን መሰረት ያደረጉ የሰብአዊ መብት ጥሰቶች ሲፈፀሙበት መቆየታቸውን የገለጹት ጀነራል አሳምነው ችአሁን ላይ የዜጎችን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ደህንነት ሊያረጋግጥ የሚችል የለውጥ ብርሃን እየታየ ቢሆንም ጥቅማቸው የተነካባቸው አካላት ለውጡን ወደ ኋላ ለመመለስ እየተንቀሳሱ መሆኑን  ገልጸው መንግስት ችግሩን በሰከነና ዘላቂነት ባለው መንገድ ለመፍታት ብርቱ ጥረት እያደረገ እንደሆነ አስታውቀዋል።

Previous Story

የጊሪና የጃርሶ ጎሳዎች መካከል የተፈጠረውን ግጭት በማቆም ዘላቂ ሰላም ለማምጣት የሚያስችል ስምምነት  ተደረገ

Next Story

በአርቲስት ፈቃዱ ተክለማሪያም ስም የተሰበሰበው ገንዘብ ኮሚቴውንም ለሁለት ከፈለው

Go toTop