Español

The title is "Le Bon Usage".

በትግራይ ክልል ላለው ወቅታዊ ሁኔታ፤ የፌደራል መንግስት “አስፈላጊውን ድጋፍ” እንዲያደርግ የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር አሳሰበ

March 12, 2025

የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር በክልሉ “በጸጥታ ኃይሎች ስም” እየተንቀሳቀሱ ባሉ አካላት፤ “የፕሪቶሪያ ውል ሲፈርስ እና የትግራይ ህዝብ ወደ ዳግም ጥፋት ሲገባ ዝም ተብሎ መታየት የለበትም” አለ። የፌደራል መንግስት እነዚህ አካላት የትግራይ ህዝብንም ሆነ ጊዜያዊ አስተዳደሩን የማይወክሉ መሆኑን ተገንዝቦ “አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ አለበት” ብሏል።

ጊዜያዊ አስተዳደሩ ይህን ያለው በትግራይ ክልል ያለውን “ወቅታዊ ሁኔታ” በተመለከተ ዛሬ ረቡዕ መጋቢት 3፤ 2017 ባወጣው መግለጫ ነው። አስተዳደሩ በዚሁ መግለጫው፤ በጥር ወር አጋማሽ ከተደረገው የትግራይ ሰራዊት ከፍተኛ አዛዦች ስብሰባ ወዲህ የተከሰቱ ጉዳዮችን ዘርዝሯል።

አስተዳደሩ “ወንጀለኛ” ከሚለው ቡድን ጋር “ወግነዋል” ያላቸው የሰሜን ምስራቅ እና ደቡብ ግንባር ሰራዊት አዛዦች፤ “ህገ ወጥ ተግባራትን” ከሰሞኑ ሲፈጽሙ መቆየታቸውን ገልጿል። እነዚህ “ህገ ወጥ ድርጊቶች” እና “አደገኛ አካሄዶች” እንዲቆሙ፤ ለትግራይ ሰራዊት ዋና አዛዥ ባለፈው የካቲት ወር መጨረሻ ትዕዛዝ ቢሰጥም፤ ይህ ሳይሆን ቀርቶ “የጥፋት ተግባራቱ” ወደ “ከፋ ሁኔታ” መሸጋገራቸውን ጊዜያዊ አስተዳደሩ በመግለጫው ላይ አመልክቷል።

ይህን ተከትሎም “በሰላማዊ ዜጎች ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች መቀጠላቸውን” ጊዜያዊ አስተዳደሩ አስታውቋል። ጊዜያዊ አስተዳደሩ ይህን ከማለቱ አስቀድሞ መግለጫ ያወጣው የደቡብ ምስራቅ ዞን አስተዳደር፤ ትላንት ማክሰኞ አመሻሽ ላይ በዓዲ ጉዶም ከተማ ነዋሪዎች ላይ “በተከፈተ ተኩስ”፤ አራት ሰዎች በከባዱ ሲቆስሉ “በርካቶች” ደግሞ ቀላል ጉዳት እንደደረሰባቸው አስታውቆ ነበር።

የዞኑ አስተዳደር በዚሁ መግለጫው፤ በትላንትናው ዕለት ከዓዲ ጉዶም ከተማ እና ከሳምረ ወረዳ ዘጠኝ አመራሮች ወዳልታወቀ ቦታ ታፍነው መወሰዳቸውንም ገልጿል። ከዞኑ አስተዳደር በኋላ የወጣው የጊዜያዊ አስተዳደሩ መግለጫም፤ በትግራይ “ከላይ እስከ ታች መንግስት ለማፍረስ የሚደረጉ ተግባራት በከፋ ደረጃ ተጠናክረው ቀጥለዋል” ሲል አጽንኦት ሰጥቷል።

“የትግራይ ሰራዊት ከፍተኛ አዛዦች የኋላ ቀሩን ቡድን ፍላጎት ለማሟላት ሲሉ መንግስት እንዲፈርስ እና የፕሪቶሪያ ውል እንዲጣስ በማድረግ፤ የትግራይ ህዝብን ወደ ዳግማዊ ጥፋት እያስገቡት ነው” ሲልም የክልሉ ጊዜያዊ አስተዳደር በመግለጫው ወንጅሏል። “የፕሪቶሪያ ውል ሲፈርስ እና የትግራይ ህዝብ ወደ ዳግም ጥፋት ሲገባ ዝም ተብሎ መታየት የለበትም” ሲል ጊዜያዊ አስተዳደሩ ለፌደራል መንግስት መልዕክት አስተላልፏል።

በትግራይ ክልል “በጸጥታ ኃይሎች ስም የሚንቀሳቀሱ” አካላት “የአንድ ኋላ ቀር” እና “ወንጀለኛ ቡድን” ተላላኪ መሆናቸውን የፌደራል መንግስት መገንዘብ እንዳለበት ጊዜያዊ አስተዳደሩ በመግለጫው ላይ አጽንኦት ሰጥቷል። እነዚህ ኃይሎች “የትግራይ ህዝብንም ሆነ ጊዜያዊ አስተዳደሩን የማይወክሉ መሆናቸውንም” የፌደራል መንግስት ሊረዳ እንደሚገባም አመልክቷል።

የፌደራል መንግስት በትግራይ ክልል ያለውን አሳሳቢ የጸጥታ ሁኔታ በመረዳት “አስፈላጊውን ድጋፍ ማድረግ አለበት” ሲልም ጊዜያዊ አስተዳደሩ በመግለጫው አሳስቧል። እነዚህ አካላት “ወንጀሎቻቸውን ለመከላከል“ ”የፕሪቶሪያ ውልን እያፈረሱ ነው” ሲል የከሰሰው ጊዜያዊ አስተዳደሩ፤ የዓለም ማህበረሰብም በተመሳሳይ ሁኔታ “አስፈላጊውን ጫና” እንዲያደርግ ጥሪ አቅርቧል።

“ይህ ሳይሆን ከቀረ ግን የትግራይ ህዝብ ሊወጣበት ወደማይችል ሌላ ዙር ጥፋት እንደሚገባ መላው ህዝባችን ሊገነዝብ ይገባል” ሲል የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር በመግለጫው ማጠቃለያ አስጠንቅቋል። በትግራይ ክልል ያለው ወቅታዊ ሁኔታ፤ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ፕሬዝዳንት አቶ ጌታቸው ረዳ ሶስት ከፍተኛ የሰራዊት አዛዦችን ማገዳቸውን ተከትሎ ከፍ ወዳለ ውጥረት ተሸጋግሯል።

ህንን የአቶ ጌታቸው ረዳን እርምጃ የጊዜያዊ አስተዳደሩ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ እንዲሁም በዶ/ር ደብረጽዮን ገብረሚካኤል የሚመራው የህወሓት ጎራ በየፊናቸው ተቃውመውታል። የክልሉ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ በትላንትናው ዕለት ባወጣው መግለጫ፤ የአቶ ጌታቸው እርምጃ “የተቋሙን አሰራር ያልተከተለ”፣ “ያልሰቀለውን የሚያወርድ” እና “የተናጠል እርምጃ” በመሆኑ ተቀባይነት እንደሌለው አስታውቆ ነበር።

የሰራዊት አዛዦቹ እግድ “ወንጀልንና ወንጀለኞችን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር እየተደረገ ያለውን ጥረት ወደ ኋላ የሚመልስ ስለሆነ በአስቸኳይ እንዲቆም” የክልሉ ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ በዚሁ መግለጫው ጠይቋል። በዶ/ር ደብረጽዮን የሚመራው የህወሓት ጎራ በበኩሉ የሶስቱን ሰራዊት አዛዦች እግድ “ብሔራዊ ክህደት” እና “አሻጥር” ሲል ጠርቶታል።

በዶ/ር ደብረጽዮን የሚመራው ህወሓት ከትላንት በስቲያ ለሊት ባወጣው መግለጫ፤ “በዚህ ወሳኝ ወቅት የሰራዊት ግንባር አዛዦችን ‘አግጄያለሁ’ ማለት ሆን ተብሎ ተጋላጭነት እንዲጨምር ለማድረግ፣ የትግራይ ህዝብን ሉዓላዊነት እና ደህንነትን አደጋ ላይ እንዲወድቅ ለማድረግ ያለመ ክህደት ነው” ሲል የአቶ ጌታቸውን እርምጃ ነቅፏል።

የዜናው ዘገባ የ ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ነው

Leave a Reply

Your email address will not be published.

Previous Story

ካሳቫ የተባለው የስራስር ዱቄት በእንጀራ ላይ ተጨምሮ እንዲሸጥ ተፈቀደ

Zehabesha | Ethiopian Latest News, Top Analysis & Best Articles <h1 style="text-align:center">tHE HABESHA Ethiopian Reliable News Source – Truth Will Win</h1><title> <title><h2 style="text-align:left">Get the Best Scholarly Articles and Analysis on ZeHabesha</h2><title> <title><h3 style="text-align:right">Zehabesha Ethiopian News</h3><title> <title><h4 style="text-align:justify">Ethiopian Lates News</h4><title> <meta name="keywords" content="Ethiopian News, Ethiopia News, Ethiopian News Today, Top Stories, The Habesha, Latest News, Ethiopia, Breaking News, zehabesha, zehabesha Amharic News, The Habesha News, Headlines, borkena. bbc amharic, repoter, mereja, Ethiopian News provider"> <!-- Google Tag Manager --> <script>(function(w,d,s,l,i){w[l]=w[l]||[];w[l].push({'gtm.start': new Date().getTime(),event:'gtm.js'});var f=d.getElementsByTagName(s)[0], j=d.createElement(s),dl=l!='dataLayer'?'&l='+l:'';j.async=true;j.src= 'https://www.googletagmanager.com/gtm.js?id='+i+dl;f.parentNode.insertBefore(j,f); })(window,document,'script','dataLayer','GTM-5WDL6STX');</script> <!-- End Google Tag Manager --> <!-- Google tag (gtag.js) --> <script async src="https://www.googletagmanager.com/gtag/js?id=G-W9E3TWE2TL"></script> <script> window.dataLayer = window.dataLayer || []; function gtag(){dataLayer.push(arguments);} gtag('js', new Date()); gtag('config', 'G-W9E3TWE2TL'); </script> <meta name="msvalidate.01" content="4781C31A916C7AB883D8AF1F4F3BFC49" /> <link rel="icon" href="/path/to/favicon.ico"> <link rel="icon" type="image/png" href="/thehabesha.com/favicon-96x96.png" sizes="96x96" /> <link rel="icon" type="image/svg+xml" href="/thehabesha.com/favicon.svg" /> <link rel="shortcut icon" href="/thehabesha.com/favicon.ico" /> <link rel="apple-touch-icon" sizes="180x180" href="/thehabesha.com/apple-touch-icon.png" /> <link rel="manifest" href="/thehabesha.com/site.webmanifest" /> <meta name="seobility" content="48b995a16caf3ab9d546a000c18b65d3"> <main> <!-- Main content of your page goes here --> </main> <script type="text/javascript" src="//cdn.rlets.com/capture_configs/d2b/aac/e54/1fc4f7ea32cf1e1d818a0f2.js" async="async"></script> <script async src="https://www.googletagmanager.com/gtag/js?id=TAG_ID"></script> <script src="https://www.googleoptimize.com/optimize.js?id=OPT-M8Z33GL"></script> <meta name="google-site-verification" content="Lf_65x5pXGn-W1TA8CsfJi-53aAyIKdfVyM_QkwpvgY" /> <head> <title>Ethiopian Latest News: Top Analysis and the best Articles<title> <script defer data-domain="thehabesha.com/mEUHSv" src="https://api.publytics.net/js/script.manual.min.js"></script> <script> window.publytics = window.publytics || function() { (window.publytics.q = window.publytics.q || []).push(arguments) }; publytics('pageview'); </script> <!-- Google tag (gtag.js) --> <script async src="https://www.googletagmanager.com/gtag/js?id=UA-215686007-9"></script> <script> window.dataLayer = window.dataLayer || []; function gtag(){dataLayer.push(arguments);} gtag('js', new Date()); gtag('config', 'UA-215686007-9'); </script> <script async src="https://pagead2.googlesyndication.com/pagead/js/adsbygoogle.js?client=ca-pub-9091845805741569" crossorigin="anonymous"></script> <script async custom-element="amp-ad" src="https://cdn.ampproject.org/v0/amp-ad-0.1.js"></script> <title>Zehabesha Ethiopian Reliable News Source – Truth Will Win