33 የአዲስ አበባ ወጣቶች በ15 ሺህ ብር ዋስትና እንዲፈቱ ፍርድ ቤት የሰጠው ትእዛዝ ታገደ

December 14, 2018

የኦነግን አቀባበል ተከትሎ በአዲስ አበባ ቡራዩና አካባቢው ከተፈጠረው ችግር ጋር በተያያዘና በሽብርተኝነት የተከሰሱት የአዲስ አበባ ወጣቶች ዛሬ ፍርድ ቤት ቀረቡ፡፡ ከቀናት በፊት 17 ያህል በተመሳሳይ ክስ የቀረቡ የከተማው ወጣቶችን ክስ ፍርድ ቤቱ ወደግድያ ወንጀል እንደቀየረው መዘገባችን ይታወሳል፡፡

በዛሬው የፍርድ ቤት ውሎ በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 4ኛ የወንጀል ችሎት 33 ተጠርጣሪዎች የቀረቡ ሲሆን መርማሪ ፖሊስም ያቀረበው ክስ ሽብርተኝነት ነበር፡፡ በዚህ መሰረት መርማሪ ፖሊስ በወቅቱ ጉዳት የደረሰባቸውን ሰዎች የሙሉ ምስክርነት ቃል ለመቀበል እንዲሁም ተጎጅዎችን በአካል ማነጋገር አስፈላጊ መሆኑን ለፍርድ ቤቱ በማስረዳት 28 ቀን ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንዲፈቀድለት ጠይቋል። የተጠርጣሪ ጠበቆች በበኩላቸው እያቀረባቸው ያለው ሀሳቦች ተደጋጋሚና የተከሳሾችን የዋስትና መብት የሚጋፋ በመሆኑ በነፃ እንዲያሰናብታቸው ወይም ደግሞ የዋስትና መብታቸው እንዲጠበቅ ፍርድ ቤቱን ጠይቀዋል።

የግራ ቀኙን ክርክር የተመለከተው ፍርድ ቤቱ የፖሊስን ጥያቅ ውድቅ በማድረግ ተከሳሾ በ15 ሺ ብር ዋስ እንዲፈቱ ትእዛዝ አስተላልፎ የነበረ ቢሆንም መርማሪውና አቃቤ ህግ ይግባኝ በመጠየቃቸው የዋስትናው ትእዛዝ ታግዷል፡፡

https://www.youtube.com/watch?v=YJYMYnduprQ&t=125s

Previous Story

ቅዳሜና እሁድ በአዲስ አበባ ሊደረጉ የነበሩት ህዝባዊ ሰልፎች ተራዘሙ

Next Story

በመቀሌ የዳቦና የስንዴ እጥረት ተከስቷል

Go toTop